Tuesday, April 30, 2013

ሰሙነ ሕማማት (ዘሰሉስ)

ማክሰኞ
ይህ ቀን ጌታችን ሰኞ በተናገረውና ባደረገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ዕለት ነው። በዚህም ምክንያት የጥያቄ እና የትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ በቅዱስ ማቴዎስ፣ በቅዱስ ማርቆስና በቅዱስ ሉቃስ አዘጋገብ መሠረት ስድስት ነገሮች በዕለተ ሰሉስ/ማክሰኞ ተደርገዋል።
እነርሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
  1. በማለዳ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ደቀ መዛሙርቱ ጌታ ሰኞ የረገማትን በለስ አይተው ሲደነቁ ስለ እምነት ትምህርት ሰጣቸው። /ማቴ 21፡ 20-22፣ ማር 11፡20-26/
  2.  ወደ ኢየሩሳሌም ገብቶ በመቅደስ ሲመላለስ ለቀረበለት የተለያዩ ጥያቄዎች መልስ ሰጠ። /ማቴ 21፡23-27፣ ማር 11፡25፣ ሉቃ 20፡1-40/
  3. ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ስክርስቶ ስለራሱ ማንነት ጠየቋቸው መልስ አሳጣቸው። /ማቴ 22፡41-46፣ ማር 12፡35-37፣ ሉቃ 20-41-44/
  4. ፈሪሳውያንን በግብዝነታቸው ምክንያት ገሰፃቸው። /ማቴ 23፡1-39፣ ማር 12፡38-40፣ ሉቃ 20፡45-47/
  5. የድኃዋን መበለት ስጦታ አደነቀ። /ማር 12፡41-44፣ ሉቃ 21፡1-4/
  6. ስለ ዳግም ምፅአት ሠፊ ትምህርት ትምህርት አስተምሯል። /ማቴ 24፡1-25፣ ማር 13፡1-25፣ ሉቃ 21፡5-36/
በዚህ ዕለት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ ስለ ሥልጣኑ ተጠይቋል፡፡ ጠያቂዎቹ የካህናት አለቆችና የሕዝብ አለቆች ናቸው፡፡ ጥያቄውም “በማን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን የሰጠህ ማነው?” የሚል ነበር፡፡ የካህናት አለቆች ያቀረቡት ጥያቄ ነበር፡፡ ጌታችን ሰኞ ዕለት ሁለት ነገሮችን ማድረጉን ተያይዞ የተነሣ ጥያቄ ነው፡፡ ሰኞ ከቅጠል ብቻ በቀር ፍሬ ያላገኘባትን ዕፀ በለስ ረግሟል፤ በማስከተል ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን አስወጥቷል፡፡ ማቴ.21÷23-25፤ ማር.11÷27፣ ሉቃ.20÷1-8፡፡ ከላይ እንደ ተገለጸው ጌታችን ሲያደርጋቸው የነበሩት ተአምራትና የኃይል ሥራዎች የካህናት አለቆችን ስላስቀናቸው ጌታችንን ከሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ለማጋጨት የቀየሱት ስልት ነው፡፡
ጌታችን በቤተ መቅደስ የነበሩትን ነጋዴዎችን አባሯል፤ መደባቸውን ገለባብጧል፡፡ ነጋዴን ማባረርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነው፡፡ በአንድ አገር የንግድ ቦታን የሚያጸድቅ መንግሥት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ጌታችን ፈሪሳውያን ላቀረቡት ጥያቄ ቀጥተኛ መልስ አልመለሰም፡፡ ምክንያቱም ጥያቄው ለከሳሾቹ አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር ጥያቄውን በጥያቄ መልሷል፡፡ “በመባሕተ መኑ ትገብር ዘንተ፤ በማን ሥልጣን ነው ይህን የምታደርገው?” ነበር ያሉት፡፡ በራሴ ሥልጣን ቢላቸው ፀረ መንግሥት አቋም አለው በማለት ከሮማ መንግሥት ዘንድ ለማሳጣት ነበር ዕቅዳቸው፡፡
ጌታችን እኩይ የሆነውን የፈሪሳውያንን አሳብ በመረዳት “የዮሐንስ ጥምቀት ከየት ነው ከሰማይ ነው ወይስ ከምድር ሲል” ጠይቋቸዋል፡፡ ከሰማይ ያልነው እንደ ሆነ ለምን አላመናችሁበትም ይለናል÷ ከሰው ያልነው ከሆነ ሕዝቡ ይጣላናል፡፡ ምክንያቱም ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ አባት ይፈሩት እንደ መምህር ያከብሩት ነበርና ከዚህ የተነሣ ያቀረቡት የፈተና ጥያቄ ግቡን ሳይመታ ከሽፎባቸዋል፡፡ 
ዛሬም ቢሆን መልካም ሥራን በሠራን ጊዜ ከልዩ ልዩ ወገኖች የሚመጡ ፈተናዎች ለመልካም ሥራችን እንቅፋት ሊሆን እንደሚችሉ መገንዘብ አለብን፡፡ ብዙ ወገኖች ለቅን አሳባችን ለምን ሰዎች ክፉ ነገር ይመልሱልናል በማለት ሲጠይቁ ይሰማል፡፡ ለቅን ዐሳባችን ከዓለም ዘንድ የተገላቢጦሽ ነገር እንደ ሚጠብቀን “ዓለም የሚወደው የገዛ ወገኑን ነው” የሚለውን የጌታችንን ትምህርት ልብ ይሏል፡፡ ይህ በመሆኑ በዘመናችን አሳልፈው ሊሰጡን የሚፈልጉ ሰዎች ፈታኝ ጥያቄ እንደሚያቀርቡልን ከወዲሁ ልንገነዘብ ይገባል

Sunday, April 28, 2013

ሰሙነ ሕማማት


ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከገባ ጀምሮ ያሳለፈውና ከትንሳኤው በፊት ያለው አንድ ሳምንት ወይም የመጨረሻ ሳምንት " ሰሙነ ሕማማት " ይባላል፡፡ በጌታ ላይ የሞት ምክር የተመከረበትና በብዙ መከራና ሕማማት ለመግደል የወሰኑበትና የተገደለበት ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህም ሰሙነ ሕማማት የሚለው ስያሜ ጌታ የተቀበለውን ፀዋትዎ መከራን ለማዘከር የሰተጠ ስያሜ ነው፡፡ የጌታ የመስቀሉ ሕማሞች ወይም " ሕማማት መስቀል " ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦ 
1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀል በችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።
በዚህ ሳምንት ውስጥ ካህናትና ምዕመናን በአፀደ ቤተ ክርስትያን ተሰብስበው ከሀጥያት ርቀው ከምግብና ከመጠጥ ተቆጥቦ በጾምና በጸሎት የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ ሲያዜሙ ግብረ ሕማም የሚባለውን መጽሐፍ እያነበቡ ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ።
ከአባታችን አዳም በደል ወይንም ስሕተት በኋላ በሕማማት፣ በደዌያት፣ በመቅሰፍታት፣ ወዘተ በብዙ መከራ የሰው ልጅ ሊኖርባቸው ግድ የሆነባቸው ዘመናት ጥቂቶች አልነበሩም፡፡ ጥሮ ግሮ ወጥቶ ወርዶ ለፍቶ ማስኖ የዕለት ጉርስ የቀን ልብስ ማግኘት እጅግ አዳጋች ነበር፡፡ ሁልጊዜ የሰው ልጅ ቢያጠፋ ቢበድል ከሕገ እግዚአብሔር ቢወጣ እንኳ የዋህ፣ ታጋሽ፣ ቸር፣ አዛኝ የሆነ አምላክ የጠፋውን ሊፈለግ የተራበውን ሊያጠግብ የታረዘውን ሊያለብስ፣ ፍቅር ያጣውን ፍጹም ፍቅር ሊለግስ፣ ሰላም ለሌለው ፍጹም ሰላም ሊሰጥ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፋ ሊያጐናጽፍ ከሰማይ ወረደ፤ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ ቀንና ሌሊት ጾመ፡፡ በጾሙም የኃጢአት ሥሮች ወይም ራሶች የተባሉትን ስስትን፣ ትዕቢትንና ፍቅረ ንዋይን ድል አደረገልን፡፡ እኛ እርሱ የጾመውን ጾም እንድናከብር እንድንጾም ምሳሌ ሆነን፡፡ ዲያብሎስን ድል አድርጐ ድል እንድንነሣው ኃይልና ምሳሌ ሆነን፡፡

ሰሙነ ሕማማት ማለት፦
ሰመነ ስምንት /ሳምንት/ አደረገ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ከዕለተ ሆሣዕና ሰርክ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ ወይም ቀናት የሚያመለክት ነው፡፡ ሐመ ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ጸዋትወ መከራዎች የሚያሳስብ ነው፡፡ ዕለታቱ የዓመተ ኩነኔ ወይም የዓመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት ቤት ንብረታቸውን ትተው ከሌላው ቀናትና ጊዜያት በተለየ መልኩ ቤተ ክርስቲያናቸውን የሚማጸኑበት፤ ጧት ማታ ደጅ የሚጠኑበት፤ ኃጢአታቸውን በቤተ ክርስቲያን አደባባይ ለካህኑ የሚናዘዙበት በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ሳምንት ነው፡፡

በዚህ ሳምንት ብዙ አዝማደ መባልእት አይበሉም፤ ይልቁን በመራብ በመጠማት በመውጣት በመውረድ በመስገድ በመጸለይ በመጾም በየሰዓቱ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጸዋትወ መከራዎች በማሰብ አብዝቶ ይሰገዳል፡፡ መከራውን፣ ሕማሙን፣ ድካሙን የሚያስታውሱ ከቅዱሳት መጻሕፍት ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ መዝሙረ ዳዊት ግብረ ሕማማት ወዘተ በየሰዓቱ ይነበባል፡፡

መስቀል መሳለም የለም፡፡ ካህናትም እግዚአብሔር ይፍታህ አይሉም የሳምንቱ ሥርዓተ ፍትሐት አይደረግም፡፡ ይኸውም ይህ ሳምንት ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገርንበት ከጨለማ ወደ ብርሃን የተጓዝንበት የመሸጋገሪያ ወቅት ምሳሌ በመሆኑ ነው፡፡ በዕለተ ምጽአት መላእክት የመለከት ድምጽ በማሰማት የዳግም ምጽአትን ዕለት ለማሳሰብ ምእመናን ጥሪውን ሰምተው ለዚህም አስቀድመው ተዘጋጅተው የበዓሉ ታዳሚዎች መሆናቸውን በማጠየቅ በዚህ ሳምንት ዲያቆኑ ቃጭል እየመታ በየሰዓቱ ምእመናኑን በጸሎት ተግተው፣ ምግባር ቱሩፋት ሰርተው፤ በይቅርታውና በምህረቱ ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን እንዲወርሱ ያሳስባል፡፡
በሰሙነ ሕማማት የሚገኙ ዕለታትና ስያሜያት
             ዕለተ ሰኑይ /ሰኞ/
ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም ሲመላለስ በሆሳዕና ማግሥት ጌታችን ከቢታንያ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ሁለት ነገሮችን አድርጓል፡፡ አንደኛ ከቅጠል በስተቀር ፍሬ ያልተገኘባትን ዕፀ በለስ ረግሟል፡፡ ሁለተኛ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን አስወጥቷል፡፡/ማቴ.21÷12-17፤ ማር.11÷17፤ ሉቃ.19÷45-46፡፡ በቅዱስ ሉቃስ ወንጌል ላይ እንደተገለጸው  ይህንም ምሳሌ አለ "ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም፡፡" ሉቃ 13፡6 በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡
 ጌታችን መድኃኒታችን ወደ ቤተ መቅደስ ግብቶ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን እንዳስወጣ ሁሉ፤ ዛሬ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ጌታችን ወደ መቅደስ ሕይወታችን ቢመጣ ምን ያገኝ ይሆን? ፍሬ ወይስ ቅጠል? የእግዚአብሔር ቃል ግን ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ ይለናል። ማቴ 3፡8 ስለዚህ አምከ ቅዱሳን ከእኛ የሚፈልገውን የመንፈስ ፍሬ እናፍራ። ገላ 5፡22 



Saturday, April 27, 2013

How to Benefit Spiritually from Passion/holy Week


How do we enjoy the most spiritual week of the year? by His Holiness Pope Shenouda III


1. Our behavior inside and outside church:


It is very noticeable that many people during Passion Week act very differently inside church than they do outside church. Inside church… black curtains, sad hymns, solemn readings, and complete concentration on the suffering of Christ. However, outside of church, we often laugh, joke around, socialize, think and talk about many worldly issues. We lose all the spiritual depth that we gained inside church. Let us concentrate our thoughts, conversations, and meditations around the events of this Holy Week and the passion of our Savior.

2. Retreat:


During our regular fasting days, we put the words of the Bible before us, "Consecrate a fast, call a sacred assembly " (Joel 1: 14). How much more then should we apply this commandment during Holy Week? This week should be characterized by solitude and retreat with God by staying away from idle discussions, various means of entertainment and pleasures. Reserve your time for God and to spiritual activities worthy of this week.

3. Follow the steps of Christ:


Meditate on the events of the week one by one, from Palm Sunday when Christ refused His worldly kingdom and the Jews gave up their hopes in Him, until they crucified and buried Him. On Palm Sunday, ask yourself: Is Christ King and Lord over everything in my life? Do I, like Christ, turn down worldly glory for spiritual and eternal glory? And during the "general funeral" afterwards, consider yourself attending your own funeral (because during this week the church will not hold funeral services). Also, when the church denounces Judas' betrayal with a kiss on the eve of Wednesday's Pascha, ask yourself in prayer, "How often, O Lord, have I betrayed You?" "How many times have I told You words of love in prayers, while my actions show the opposite and my heart is far away from You?"

4. Share in the fellowship of His suffering:


St. Paul said "That I may know Him and the power of His resurrection, and the fellowship of His suffering, being conformed to His death" (Philippians 3:10). Can we give ourselves an exercise this week to share in the fellowship of His suffering and be conformed to His death? (source of this article: St-Takla.org) Can we follow Him in His suffering and ascend with Him to the cross? Can we say with St. Paul "With Christ I have been crucified; it is no longer I who live, but Christ lives in me" (Gal. 2:20). Therefore, in order for Christ to live in us, we have to carry our cross and follow Him. If you have a cross in your life, don't complain about it, but rather rejoice in it and bear it for Christ’s sake. "For to you it has been granted on behalf of Christ, not only to believe in Him but to suffer for His sake" (Phil. 1:29).

5. Asceticism:


Whoever puts the suffering of Christ before Him will not take any pleasure in eating, drinking or pampering the body. But in order to succeed in pursuing asceticism,

we must satisfy our souls with spiritual food so that it may thrive and overcome physical hunger.

6. Spiritual readings:                                                         


Spiritual readings are also food for the soul. The church has organized for us a treasure of appropriate readings for every day of Holy Week. This consists of Gospel readings, Old Testament prophecies that correspond to the events of each day, spiritual explanations and sermons of the church fathers and on Holy Saturday (Apocalypse night) the church reads the entire book of Revelation.

7. Hymns:                                                                           


The hymns of Passion Week are moving and full of spiritual depth. Also, Hymns, like reading, preserve thoughts from wandering and guides them in a spiritual dire.

8. Prayer:                                                                            


Since the prayers of the Agpeya are not used during Holy Week, we are to substitute personal prayers in their place. This is in addition to the intensive prayers of the church asking the Lord, who bore the sins of the world and died for us, to forgive and have mercy upon us according to His great mercy.


Friday, April 26, 2013

ማነው ጥፋተኛ


ይህ የሁለት ባለትዳሮች እውነተኛ ታሪክ ነው። ለእኛም አስተማሪ ሊሆን ስለሚችል ስማቸውን ሳልጠቅስ ታሪካቸውን በአጭር አስፍሬዋለሁ።
ለሚስት የተለያዩ መስፈርቶች ቢኖራትም በዋናነት ለእርሷ ባል ማለት ከጓደኞቹ ጋር አምሽቶ የሚገባ፣ ሳያበዛ በትንሹ የሚጠጣና አንዳንዴ ካልሆነ በስተቀር በጊዜ እቤቱ የማይገባ ነው። ባል ተብየው ደግሞ ይህ አይነት ፀባይ አይመቸውም። ምንም አይነት ሱስ ስለሌለበት ማምሸትም ሆነ ከቤቱና ከባለቤቱ ውጭ የሚያስደስተው ነገር የለም። ይህ ፀባዩ ሚስቱን ብቻም ሳይሆን ከጓደኞቹም ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዳይኖረው እንቅፋት ሁኖበታል። ሚስቱ በጊዜ በመጣ ቁጥር ጭቅጭቅና ንትርክ ታበዛበታለች ለምን እንደጓደኞችህ ተጫውተህና አመሻሽተህ አትመጣም ትለዋለች። እርሱም በተደጋጋሚ እንደማይመቸውና ጥሩም እንዳልሆነ እንዲሁም የሚያስደስተው ከርሷ ጋር ማምሸትና ከሥራ ውጪ አብረው ማሳለፍ እንደሆነ ደጋግሞ ቢነግራትም ልትረዳው አልቻለችም።
ብዙ እህቶችና ወንድሞች ባለቤታቸውን ወይም እጮኛቸውን እንዲህ ብታደርግ/ብታደርጊ ደስ ይለኛል፤ እንዲህ አይነት ፀባይ ያስደስተኛል ሲሉ ይሰማሉ። እኔ የምወደው ፀባይ እንዲህ አይነት ነው እያሉ ብዙዎች መስፈርት ያወጣሉ። ነገር ግን መስፈርታቸው ወይም የሚፈልጉት ፀባይ ለትዳር ህይወታቸ  ይጥቅማል ወይስ አይጠቅምም ብለው ትኩረት የሚሰጡ በቁጥር እጅግ አናሳ ናቸው። መታየት ያለበት ግን የሚያስደስተን ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ለትዳር ህይወታችን፣ ለጓደኝነታችን፣ ለማህበራዊ ግንኝነታችን፣ ለቤተሰባዊ ፍቅር ወዘተ ጥቅም አለው ወይስ የለውም የሚለው ነው። እኔን የሚያስደስተኝ የትዳር አጋሬን ያስደስተዋል/ያስደስታታል ወይስ ያስከፋዋል/ያስከፋታል የሚሉ ጥያቄዎችን በደንብ ማየትና መመርመር ያስፈልጋል። ከትዳር አጋራችን የምንፈልገው መስፈርት በመካከላችን  መተሳሰብ፣ ውይይትና ፍቅር የተሞላበት እንዲሆን ምክንያት የሚሆኑ ነገሮች ላይ ትኩረት ማድረግ ተገቢ ነው። ከዚህ ከአለፈ ግን ከሰላም ይልቅ ጠብና ክርክር፣ ከአንድነት ይልቅ መለያየት፣ ከመተሳሰብ ይልቅ ግደለሽነት ሊያስገባን ይችላል።
የእነዚህ ባለትዳሮችን ህይወት ስንመለከት የሚስትን ጭቅጭና ለእርሱ የምትሰጠው አክብሮት የቀነሰ ስለመሰለውና እሷን የሚያስደስታት ከሆነ ከጓደኞቹ ጋር ቀስ በቀስ ማምሸት ጀመረ። በዚያን ወቅት የነበረ አንድ ወንድም እንደነገረኝ ሰውየው መጠጥ የመጀመሪያው ስለነበረ እጅግ ቢራው ከመምረሩ የተነሳ ለመጠጣት የቀመሰውን ቢራ እንደተፋው የአይን ምስክር ሁኖ ይናገራል። ሆኖም ግን ቀስ በቀስ መልመዱ አልቀረም ለመደ። ሚስት ባለቤቷ አመሻሽቶ በመምጣቱ እጅግ ተደሰተች። የኔ ባለቤትም እንደሌሎች ወግ ደረሰው እያለች መኩራራት ጀመረች።
"ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም" እንደሚባለው ከጊዜ ወደጊዜ ሰውዬው መጠጥን ጓደኛው አደረገው፤ እጅግም ተዋህደው። የዚህን ጊዜ ሚስት ተብየዋ እሷ ከምትፈልገው ስዓት ዘግይቶ ስለሚመጣ ደስታዋ ብዙም አልዘለቀም። አሁንም ተመልሳ ወደ መጀመሪያው ጭቅጭቅና ንትርክ ገባች፤ ለምን በጊዜ አትገባም፣ እኔ የተወሰነ አምሽተህና ከጓደኞችህ ጋር ተጫውተህ እንድትመጣ እንጂ እንደዚህ ዘግይተህና ሰክረህ ይባስ ብለህ አድረህ እንድትመጣ አልነበረም የኔ ፍላጎት ማለት ጀመረች። ባለቤቷ ግን በመጠጥ ሱስ  ተይዟልና ሊሰማትና ቃሏንም ተግባራዊ ማድረግ አልቻለም።
ዛሬ ላይ ትዳራቸው እጅግ አስከፊና አደጋ ላይ ወድቋል። የወር ደሞዙን ከመቀበሉ በፊት ይጨርሰዋል። በቤታቸው ሰላም የሚባል ነገር ጠብና ክርክር ነግሦአል። "ድሮ  ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ" እንደሚባለው እሷ የዘወትር ስራዋ ማልቀስና አምላኳን ማማረር ሁኗል። ለዚህ ጥፋት ተጠያቂው ማነው? ሚስት ወይስ ባል? እኛስ የምንፈልገው መስፈርት ለትዳራችን ምን ያክል አስተማማኝ ይሆን?

እንወያይበት

Tuesday, April 23, 2013

የተግባር ፍቅር


ፍቅርን የሃይማኖት አባቶች፣ የፍልስፍና ሰዎችና ዘመናዊ ወጣቶች በተለያየ መልኩ ይገልጹታል፤ እኛም ሁላችን ፍቅርን ግለጹ ተብሎ ጥያቄ ቢቀርብልን በተረዳነው መጠንና በሚመቸን መልኩ እንገልጸዋለን። ነገር ግን የገለጽነውን፣ የተረጎምነውን፣ የተረክነውን በተግባር መኖር እንችላለን ወይ የሚለው ለሁሉም ሰው ትልቅ ጥያቄ ነው።
ስለ ፍቅር መጻፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት እስከ እራይ ዮሐንስ በግልጽና በምንረዳው መልኩ ተገልጾልናል። ብርሃን ዓለም ቅዱስ ጶውሎስ ስለ ፍቅር በአስተማረበት አንቀጹ በ1ኛ ቆሮ 13፡1 ጀምሮ_ ፍቅርን በሚገባ ከተረጎመው በኋላ "እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ፍቅር ግን ከሁሉም ይበልጣል። ዛሬ ላይ የሁሉ ሰው ጥያቄ ሊሆን የሚገባው ይህን ከሁሉ የሚበልጠውን ፍቅርን ምን ያክል በተግባር እየተገበርነው ነው? በምን መልኩ እየኖርንበት ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ይገባናል።
  ዓለም ይህን ታላቅ የእግዚአብሔር ስጦታ በተግባር ተግብሮ የሚያሳያት ብታገኝ ኑሮ ባልጠፋች፤ ከብርሃን ወደ ጨለማ፣ ከሰላም ወደ ጠብና ክርክር፣ ከጽድቅ ወደ ኩነኔ፣ ባአጠቃላይ ወደ መከራ፣ ችግር፣ረሃብ፣ ቸነፈር፣ ጦርነትና ራስን ማጥፋት ደረጃ ባልደረሰች ነበር።
በትዳራችንና በጓደኝነታችን መካከል ወደድኩሽ፡ ወደድኩህ፣ ወደድኩህ ወደድኩሽ ከሚለው አልፈን ፍቅርን በተግባር መተግበር ብንችል ትዳራችን እንደ አብርሃምና ሳራ ተብሎ እንደተዘመረልን ሰላምን፣ ደስታንና መተሳሰብን ተጎናጽፈን እከመጨረሻው የጸናን እንሆን ነበር ዳሩ ግን ፍቅራችን የንግግር እንጂ የተግባር ስላልሆነ ፍቅር ከመካከላችን ቀዝቅዛ ዓለም በምቀኝነትና በጥላቻ ወድቃ፤ በትዳራችንና በእኛነታችን ውስጥ ያለው ፍቅር የታይታና የውሸት ፍቅር እየሆነ በመምጣቱ መተማመን እንዲጎለን አድርጎታል።
አባቶቻችን ስለፍቅር ሲናገሩ፡ "ፍቅርን ይኖሩታል እንጂ በቃላት አይገልጹትም" ብለው ፍቅርን በተግባር እንጂ ለሰዎች ማሳየት/መግለጽ የምንችለው በቃላት፣ በንግግር፣ በሐተታ መግለጽ እንደማይቻል ያስረዳሉ። ፍቅርን በተግባር የሚተገብሩ ምንኛ የታደሉ ናቸው? ምክንያቱም ፍቅር ማለት ራሱ እግዚአብሔር ነውና። «እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፡ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል» 1ዮሐ 4፡16። ሁላችንም ቢሆን ፍቅርን በቃላት እናውቀዋለን፣ እንናገረዋለን፣ እንተርከዋለን ነገር ግን ተግባር ላይ የለም፤ አንኖርበትም። እግዚአብሔር አምላክ እንደሚወደን፣ እንደሚያፈቅረን ነገረን በተግባር በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ነፍሱን ስለኛ ሲል በፈቃዱ ሰጦ ፍቅርን ገለጸልን። እኛ ዛሬ የዘመኑን የሀሰት ፍቅር ከየት አመጣነው? ከማን ወረስነው? መጨረሻችንስ ምን ይሆን? እና መሰል ጥያቄዎችን ለመመለስ የተግባር ፍቅር ያስፈልገናል።

የተግባር ፍቅር ከአባቶች፦ አባቶቻችን በትምህርታቸው፣ በስብከታቸው፣ በንግግራቸው ሁሉ ፍቅርን ይገልጻሉ። ነገር ግን ፍቅርን በተግባር ተግብሮ የሚያሳየን አባት ያስፈልገናል። አርያና ምሳሌ የሚሆን አባት ለቤተ ክርስቲያን፣ ለመንግሥትና ለዓለም ያስፈልጋል። አባቶች ፍቅር በተሞላ አገልግሎታቸው ዓለምን የመለወጥ ጸጋውም ልምዱም ብቃቱም አላቸው ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረ "ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?" ገላ 3፡1 ፍቅርን በተግባር በእውነት እንዳንተገብር ፖለቲካው፣ ዘረኝነቱና አለማዊነቱ አዚም ሁኖብናል። አባቶች ዓለም ከዚህ እንድትወጣ ቁልፉ እናተ ጋር ነውና በጸሎታችሁና በፍቅር ሳቡን፤ እኛ ዓለሙንና ምኞቱን ወደናልና ዘላለማዊ ሞትና መከራ እንዳያገኘን።
የተግባር ፍቅር ከመምህራንና ከሰባኪያን፦ እውነት ነው በሁሉም የመድረክና የጉባኤ አስተምሯችሁ ላይ ፍቅርን በአንደበታችሁ ትመሰክራላችሁ። ነገር ግን ፍቅርን በተግባር የሚያሳየን መምህርና ሰባኪ እኛ ተማሪዎቻችሁና ተሰባኪያን እንፈልጋለን። ፍቅርን ከቃላት ይልቅ ተግብራችሁ አሳዩን፤ ፍቅርን በስብከታችሁ ብቻ ሳይሆን በህይወታችሁ አሳዩን፤ አርያና ምሳሌ ሁኑን። የዘመኑ ትውልድ መስማት ብቻ ሳይሆን ማየት ይፈልጋል፤ ማስረጃን ይሻል። የአማላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ሰባኪዮች ናችሁና እንደ አምላካችን እያደረጋችሁና እየተገበራችሁ "ከእኔ ተማሩ" ልትሉን ይገባል።
የተግባር ፍቅር ከመንግሥት፦ መንግሥት ሆይ መንግሥት ከአለህዝብ ሊኖር አይችልምና ለግዛትህ ምክንያት የሆነልህን ህዝብ በፍቅር ግዛው። ህዝቤን እወዳለሁ ብለህ በአንደበትህ በመገናኛ ብዙኃን እንደምትነግረን በተግባር አሳየን። መድሎው፡ ሙስናው፡ዘረኝነቱና በቀሉ ይቅርና እንደምትወደን በተግባር አሳየን። ሁሉም ብሄር፣ ሁሉም የእድሜ ክልል፣ የተማረ ያልተማረ ለግዛትህ ያስፈልግሃልና በህዝብህ ላይ መከራና ስቃይ አታብዛብን። መንግሥት ሆይ "ሺህ ዓመት ንገሥ" ብሎ ህዝህ የሥልጣን ዘመንህን እንዳራዝምልህ ፍቅርን በተግባር አሳየን።
የተግባር ፍቅር ከሁላችን፦ "እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይቺ ናት" ዮሐ 15:12 ብሎ አምላካችን እንዳስተማረን ማንንም ሳንመለከት በመስቀል ላይ የተሰቀለውን የክርስቶስን ፍቅር እየተመለከትን ሁላችንም እርስ በእርሳችን እንዋደድ፣ እንፋቀር። ፍቅርን በተግባር ተግብረን ለሌሎችም አርያ እንሁን።

የፍቅር ሰው እንድንሆን የአምላካችን መልካም ፈቃድ፤ የቅዱሳን ተራዳኢነት አይለየን።

Monday, April 22, 2013

Protest fundraising about Abay's dam in Norway


Police stopped meeting in Tasta bydelshus, Stavanger Norway 

The police came out with three cars and six policemen and stopped a meeting of Tasta bydelshus where the atmosphere was becoming so very testy among the more than 300 attendees
The approximately 300 attendees were Ethiopian asylum seekers or people with Ethiopian background. The police feared that it would get completely out of control when people in the audience went to the hard verbal confrontation against two representatives from the Ethiopian Embassy in Stockholm who had called for and chaired the meeting.
The police gave the first message that all protesters to leave the meeting while the two embassy people and their potential supporters can be seated.This denied the attendees protesters, and several feared it would come to an open confrontation between police and people in the audience. Then, specific efforts manager Øyvind Sveinsvoll of Rogaland police to stop the meeting and clear the room.
It was a wise decision, said several of those present protesters. They did not want the two embassy people should be left as "victors" while they were evicted.
- Our goal was to stop the meeting. We managed, says one of them to Eve magazine.
ARTICLE CONTINUES BELOW THE PICTURE
Many of those in the audience spoke up and told about relatives who had been imprisoned, killed or who have disappeared in police custody.

Many of those in the audience spoke up and told about relatives who had been imprisoned, killed or who have disappeared in police custody.
PHOTO: Jarle Aasland

Had to isolate embassy people

The atmosphere was tense that the police chose to isolate the two embassy people from the rest of the participants. They escorted them out to a private car that carried them away from the area. The 300 attendees were then drop out of the courtroom.
There was general consul at the Ethiopian Embassy, ​​Abay Mebrat Beyene, who would chair the meeting with embassy secretary. The main theme was collecting money in the Ethiopian exile to a very controversial oppdemningsprosjekt - a prestige project for the regime in Ethiopia.

Mass demonstrations abroad

The Ethiopian authorities have tried to keep similar "recovery meetings" both in South Africa, Saudi Arabia, the U.S. and Germany, and each time meetings have ended in massive demonstrations against human rights violations in Ethiopia. People imprisoned without trial, free elections are abolished, freedom of speech likewise, newspapers are state controlled and many journalists imprisoned.

Not voluntary payment

Several took the floor during the meeting the key bydelshus and said this was not a voluntary fundraising. Those who did not pay the money, you could expect problems when they contacted the embassy to obtain a passport or ID papers.

Gearing up for the Oslo-riot

Saturday's meeting was the first of its kind in Norway. And exiled Ethiopians came in separate buses from Oslo, others came from Steinkjær, Otta, Stord and Bergen to demonstrate in Tasta bydelshus against the regime in Ethiopia.
28th April, the Ethiopian Embassy in Stockholm hold a similar meeting in Oslo.
- We are going to fill the buses with protesters, said several of those present to Eve magazine.
Overall, we can conclude that the government has no accepted by its peoples especially out of the country and couldn't understand the peoples feeling. Really the Ethiopian people need a dam currently? is it better to talk about fundraising or freedom? why not we are talking the current situation that the evication of Amharic speakers from the Northern part of Ethiopia? These are such a basic questions from most of us and we need answer from the government/ if there is/ rather talking about dam or something else. 

Tuesday, April 16, 2013

የኢትዮጵያ ማነቆዎች


ኢትዮጵያ በቀላሉ ሊቀረፉ በማይችሉ ሁለት አጣብቂኝዎች ውስጥ ገብታለች። ኢትዮጵያ በአንድነቷ፣ በጀግንነቷና በበርካታ ታሪካዊ ክስተቶችና ሁነታዎች የምትታወቅ ቢሆንም የአሁኑ ትውልድ ግን በሁለት ከባድ ፈተናወች/አጣብቂኝዎች/ ውስጥ ገብቶ አንዱን ክንፉና አንዱን እግር እንደተሰበረ አሞራ መብረርም መጓዝም አቅቶት ሲቃትት ይታያል። እነዚህ ማነቆዎች ሰብረን መውጣት ከአልቻልን ነገና ከነገ በኋላ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ በአንደበቱ የሚመሰክር ትውልድ እንደሚጠፋ ምንም ጥርጥር የለውም ከእዚህም አልፎ ኢትዮጵያ በኢትዮጵነቷ የመቀጠሏ እጣ ፈንታ አስቸጋሪ እንደሚሆን ነብይነት የሚሻ ጉዳይ አይመስለኝም።
ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ሊያሰኛት የሚችለው እምነቷ፣ ባህሏ፣ አንድነቷ በአጠቃላይ ከእነሙሉ ታሪኳ ስትኖርና ወደፊትም ስትጓዝ ብቻ ነው። ከዚህ በአለፈ ግን አዲስ ኢትዮጵያ እንጂ አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ሰንደቃላማዋን የአውለበለቡላት ያቺ ታሪካዊዋ ኢትዮጵያ አትሆንም። ዛሬ ላይ ያለነው ትውልድ ግን ይችን አገር አባቶቻችን በአስረከቡን መልክ ሳይሆን እየኖርንባት ያለነው አዲስ ገፅና አዲስ መልክ ሰጠን አገራዊ ወኔ ጠፍቶብንና ኢትዮጵያዊ ማንነታችንን አጥተን የምራቡን ባህል ተከትለን ልንወድቅ በመንገዳገድ ላይ እንገኛለን። ተቀምጠው የሰቀሉት ቁሞ ለማዉረድ ያስቸግራል እንደሚባለው ዛሬ ላይ ዝም ብለን ያየነው ነገር ነገ ለማስተካከልም ሆነ ለአገሩ የሚያስብ ዜጋ ለማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው። ምንም እንኳ ይህ ችግር የሚያሳስባቸው እና  እንቅልፍ የሚነሳቸው በርካታ እውነተኛ የኢትዮጵያ ልጆች በተዋበ ስነ ጽህፋዊ አጻጻፍና ከመረጃ ጋር የጻፉ ቢኖሩም እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ችግሩ ስለሚመለከተኝና ስላሳሰበኝ እነዚህ ለኢትዮጵያ ከባድ ማነቆዎችን እና መፍትሔዎችንም ለመጠቆም ወደድኩ።
እነዚህ ሁለት ማነቆዎች ብዬ በርዕሴ ላይ ያስቀመጥኳቸው ዘረኝነትና ግሎባላይዜሽን/Globalization/ ዓለም አቀፍ ትስስር ናቸው። እንዲሁ ከላይ ስንመለከታቸው ብዙም ፈታኝና አስቸጋሪ ላይመስሉን ይችሉ ይሆናል። ነገር ግን በጥልቀትና በስፋት ከአየናቸው በጣም አስቸጋሪና አሳሳቢ ጉዳዮች እየሆኑ ከመጡ ዘመናትን አስቆጠሩ።

1.     ግሎባላይዜሽን/Golobalization/

የነገ አገር ተረካቢ የምንለው ትውልድ በዘረኝነት የቀረውም በግሎባላይዜሽን ውስጥ ገብቶ ለኢትዮጵያዊነት የማይጨነቅ፣ የማይገደውና የማያስብ የኢትዮጵያንም ታርክ ማወቅ የማይፈልግ ትውልድ እየሆነ ከመጣ ዘመናትን አስቆጠረ። በእርግጥ ግሎባልይዜሽን በጥበብና በማስተዋል መቀበልና መተግበር ቢቻል ለአገር እድገት በር ይከፍታል እንጂ ጉዳቱ ባልጎላ ነበር ምንም እንኳ ኃያላን አገሮች የራሳቸው  የሆነ ውስጣዊ ትልዕኮ ቢኖራቸውም፤ ዳሩ ግን እኛ በትክክለኛ ዓላማው ሳይሆን በሌላ በኩል እየተጓዝን ስለሆነ ነው አስቸጋሪ እና ማነቆ ብዬ ከዘረኝነት ጎን ማስቀመጥ የፈለኩት። ኃያላን አገሮች ዓለምን እየመሩና በእነርሱ ስር ለማድረግ ይመቻቸው ዘንድ ትናትና በቅኝ ግዛት የራሳቸውን ባህልና እምነት በግድና በግፍ ለማስፋፋት እንደሞከሩት ሁሉ ዛሬ ደግሞ በዘመናዊ መልክ ግሎባላይዜሽን ብለው የእነርሱን ባህልና እምነት በውዴታ እንድንቀበለው እያደረጉን ይገኛሉ። እኛ ኢትዮጵያውያን ደግሞ የራሳችን የሚያኮራ ባህል፣ እምነትና ታሪክ ያለን እንጂ ከሌላ የምንዋስበት ምንም ምክንያት የለንም። በነገራችን ላይ የአደጉ አገሮችን ብንመለከት በእድገት ደረጃቸው ሁሉ ባህላቸውን፣ታሪካቸውንና ቋንቋቸውን ጨምረው ነው ያደጉት እንጂ የእነሱን በመተው በሌላ ባህልና ታሪክ አይደለም ያደጉት።በእርግጥ ዛሬ ዛሬ የአደጉ አገሮች በደመ ነፍስ ብቻ የሚንቀሳቀስ ትውልድ በመገንባት ውድድር ላይ ናቸው።
ዛሬ የኢትዮጵያ ወጣት ስለ ምዕራቡ ዓለም የሚያውቀውን ሩብ ያክል ስለ ኢትዮጵያ አያውቅም። የሌላ አገር ታሪክ ማወቁ ባልከፋ  ነበር ግን የራሳችንን ታሪክና ባህል መናቅና ማንቋሸሽ ከየት የተማርነው ታሪክ ነው፣ ወደየትስ እየተጓዝን ነው? የትስ ለመድረስ ነው? ባህልና ታሪክ የሌላትን አገር ለመመስረት? የትናት አኩሪ ታርኳን ረስተን ሌላ ኢትዮጵያ ለመመስረት? የመከባበረ፣የመቻቻል፣ የመረዳዳት፣ አብሮ የመብላት ባህሏን ረስተን ሌላ የማናውቀንና የምዕራባውያንን ባህል ለማሳደግ? ግሎባላይዜሽን እንዲህ ከሆነ ባህልን፣ ታሪክን፣ እምነትንና ቋንቋችንን የሚደበላልቅብን ከሆነ ባናድግ ቢቀርብን ይሻለናል። “ጎመን በጤና” ይላል ያገሬ ሰው እውነት ነው ያገኙትን በሰላም፣ በፍቅርና በጤና እየበሉ የአገርን ባህልና ታሪክ እየጠበቁ መኖር ታላቅ ጀግንነት ነው። ታሪክ ነውና አይረሳም ትናት መንግስት ሳይቀር ግብረ ሰዶምን ለማስፋፋትና ለማበረታታት የውጭ አገር ግብር ሰዶማውያንን እንዲዎያዩና እንዲመካከሩ ኢትዮጵያን ባርኮ  ሰጣቸው፡፡ በእርግጥ አይደንቅም ትውልዱ የምዕራብያውያንን ባህል ቢናፍቅ ምክንያቱም መንግስት በኢትዮጵያ ባህል ፈጽሞ የማይታሰበውን ድርጊት እንዲወያዩባት አገራችንን ከፈቀደ። ለዚህ ትውልድ መጥፋት ተጠያቂው ማነው? ምናልባት በዋናናት ተጠያቂ የምናደርገው አንድ አካል ልንል እንችላለን ነገር ግን ሁላችንም በትንሹም ቢሆን ከተጠያቂነት አናመልጥም። ምክንቱም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ፤ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ ለችግሩ መባባስ አስትዋጾ እያደረግን ስለሆነ። ር ሃላፊነትን ለመወጣት በትንሹም ቢሆን ይህን ትውልድ ባገኘነው አጋጣሚ ኢትዮጵዊነቱን እንዳይለቅ ማስተማርና ማስረዳት እንዲሁም ዘመናዊነትን በትክክል ከባህላችን ጋር አስተሳስሮ አብሮ እንዲያስኬደው  ትውልዱን የማስረዳት ሂደት ከእያንዳንዳችን የሚጠበቅ ታላቅ ተግባር ነው።
2. ዘረኝነት
መቼም ስለ አንድነት ለኢትዮጵያ ህዝብ መናገር ለቀባሪ ማርዳት እንዳይሆንብኝ እፈራለው። ሁላችንም እንደምናውቀው አንድነት ማለት መለያየት፣ መከፋፈልና መጠቋቆም የሌለበት ህብረት፤ እንዲሁም ለአገርና ለወገን እድገትና ብልፅግና በጋራ መስራት ማለት ነው። ዘመናዊና አገር ተረካቢው ትውልድ ግን እየተጓዘ  ያለው ከዚህ ፈጽሞ ተቃራኒና በተለየ አካሔድ ነው። ዛሬ አዲሱ ትውልድ እንደ ኢትዮጵያነታችን ሳይሆን እያሰብን፣ እየሰራን ያለነው፤ በብሔር፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በሃይማኖትና በቋንቋ ፍጹም ተለያይተን እንደ አንድ አገር ህዝብ ማሰብና መናገር ተስኖናል። ይህ አካሄድ ደግሞ በዚሁ ከቀጠለና ችግሩን ከወዲሁ መፍታትና ማስቆም ካልቻልን ለአገራችን ኢትዮጵያ እጅግ አስቸጋሪና መድኃኒት የሌለው በሽታ እንደሚሆን ዛሬ ላይ የምናያቸው ነገሮች ከበቂ በላይ ማስረጃዎች ናቸው። ለአገራችን ማነቆ ብዬ ርዕስ የሰጠሁበት ምክንያትም ይህን ጠባብ አመለካከታችንን በቀላሉ ትተን ወደ ቀደመ አንድነታችን ለመመለስ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ የሚጠይቅ በመሆኑ ነው። ጎሳዊና አካባቢያዊ ስሜታችንን ትተን ወደ አገራዊ ስሜት ከአልተሸጋገርን፣ መለያየትን ትተን አንድነትን ከአልሰበክን፣ መጠቋቆርና መተቻቸትን ትተን መተራረምንና መረዳዳትን ባህል ከአላደረግን፣ በቋንቋ በዘርና በሃይማኖት መለያየትንና መከፋፈልን ትተን ለአገር እድገትና ብልጽግና ህብረት መፍጠር ከአልቻልን በቀላሉ የወጋን እሾህ በቀላሉ አይነቀልም። ይባስ ብሎ እያመነቀዘ አካለ ጎደሎ ሊያደርገን ይችላል እንጂ። ስለዚህ ከወዲሁ ከምንም በላይ ትኩረት በመስጠት ሃይ ልንለው የሚገባ ተግባር ነው ባይ ነኝ።
ይህ የዘረኝነት በሽታ በጣም አሳሳቢና አስከፊ መሆኑን የምንረዳው የነገ አገር ተረካቢ ትውልድ የእውቀት ባለቤት ሁኖ ይወጣበታል ተብሎ በሚታሰብበት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሳይቀር በዚህ የዘረኝነት መንፈስ መጠቃቱ ነው። ተማርዎች ብቻ ሳይሆን መምህራንም ሳይቀሩ በዚህ በሽታ መለከፋቸው ችግሩን ይበልጥ ትኩረት እድንሰጠው አመላካች ነገሮች ናቸው። በሚገርም ሁኔታ ግን የአልተማረው የህብረተሰብ ክፍል የዚህ ችግር ተጠቂ አይደለም ብሎ መናገር ይቻላል፤ እዚህ ላይ ግን ሁሉም የተማረው ክፍል የዘረኝነት መንፈስ አለበት እያልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ። እንዳው ብዙ አወራህ እንዳትሉኝ እንጂ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ለዘረኝነት መንፈስ መስፋፋት ትልቅ አስትዋጾ እያደረጉ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። አንድ የከፍተኛ ት/ት ተቋም ተማሪ የሚያጠናውን የት/ት መስክ ጨርሶ በሚመረቅበት ወቅት በዘረኝነት መንፈስም አብሮ  ጎን ለጎን እንደሚመረቅ ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ የሚያሳያቸው እንቅስቃሴዎች ማስረጃዎች ናቸው። ስለዚህ መንግስትም ሆነ/የትኛውን መንግሥት እንዳትሉኝ እንጂ/ ሁላችንም ጉዳዩ ለአገር በጣም አደገኛ ስለሆነ በከፍተኛ ት/ት ተቋማት ላይ ልዩ  ትኩረት በመስጠት የዘረኝነት መንፈስ ሊቀንስ የሚችልበትን ሁኔታ ማየቱና አስፈላጊ የሆነ ጥናት መደረግ አለበት የሚል አቋም አለኝ።
እንዲሁም ለአገራችን ኢትዮጵያ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው በውጭ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዋን ከአገር ውስጥ በከፋና በባሰ ሁኔታ በዘረኝነት በሽታ በክፉ ተጎድተዋል። በዚህ በውጭው ዓለም እናተ እና እኛ እያሉ የሚያወሩ የዘረኝነትን በሽታ በወረርሽኝ መልክ የሚያስፋፉ ብዙዎች እንዳሉ በተለያየ መልክ ከማገኛቸው ሰዎች ተመልክቻለው፤ ስምን እና የሚያወራውን ቋንቋ ከሰሙ በኋላ እነሱ ከሚፈልጉት ወገን ከአልሆነ ፊታቸው የሚጠቁርና ደስቶኞች የማይሆኑም በቁጥር ጥቂቶች አይደሉም። ግን እስከ መቼ በዚህ መልኩ እንቀጥላለን? የሚለው ጥያቄ መልስ ባላገኝም የዘወትር ጥያቄዬ ነው።
እጅግ የሚገርመው ደግሞ ሃገር እመራለሁ እያለ ያለው መንግሥታችን የብሔር እኩልነት እያለ ሲያዎራ ትንሽ አለማፈሩ ነው። በእውነት ሁሉም ብሔሮች በመንግሥት በኩል እኩል ናቸው??? እንደ እኔ ግን የብሔር እኩልነት ተብሎ  ከሚወራ የብሔር ልዩነት ተረጋግጧል ተብሎ ቢወራ ሥራቸውን በሚገባ ይገልጠዋል ብየ አስባለሁ። ትናት እና ከትናት በስተያ በይፋ የተፈጸመው የብሔረ አማራ ከቦታቸውና ከአገራቸው መፈናቀል ዘረኝነቱ ምን ያክል ጎልቶ  እንደወጣ ጥሩ ማሳያ ነው። እንግዲ እኛም ዘረኝነቱ ያለብን ሰዎች የመንግሥት ዋና አስፈጻሚ አካላት መሆናችንን መገንዘብ ይኖርብናል።
አንድ ያጋጠመኝን ገጠመኝ ላውራችሁ። በስደት የምኖርበት አካባቢ ከዋናው ከተማ ትንሽ ወጣ ይላል፤ ለዋናው ከተማ አዲስ ነኝ ማለት እችላለው። በትራንስፖርት ምክንያት አልፌበታለው እንጂ ብዙ አላውቀውም። አንድ ቀን ከምኖርበት ከተማ ወደ ዋናው ከተማ ለግል ጉዳይ ሄድኩኝና አውቶብስ ተራ/ buss station/ አካባቢ ሰው እየጠበኩ ቁሚያለው፤ አበሻ ማየት በዛን ስዓት ለእኔ ብርቅ ሁኖብኛል ምንም እንኳ በመልክ አበሻ የሚመስል ሰው ባይም አይኑን ወደ እኔ የሚያዞር ማንም አልነበረም። እኔም የአገሬን አውቶብስ ተራ እያሰብኩ እስካሁን እዛ ብሆን ኑሮ የስንት ሰው አይን ያርፍብኝ ነበር እያልኩ በትዝታ አገር ቤት ገብቻለው። በዚህ ሁኔታ እያለው አንድ በእድሜ ሸምገል የአሉ ሰውዬ ከርቀት አየሁኝ። አበሻ ለመሆናቸው ከቁመና እስከ መልካቸው ይናገራል።  እኔም እንደማነኛውም ሰው ዝም ብለው ያልፋሉ ብዬ ብዙም ትኩረት አልሰጠዋቸውም ነበር፤ እርሳቸው ግን ያ የናፈቀኝን የአበሻ ፈገግታ ከቅርብ እርቀት ቸሩኝ እኔም በደስታ የፈገግታውን አፃፋ ጋበዝኳቸው። እርሳቸውም ወደኔ ጠጋ አሉና የመጀመሪያውን ማንኛውም ሰው የሚጠይቀውን ጥያቄ “አበሻ ነህ” ብለው ጠየቁኝ። እኔም ኢትዮጵያዊ አክብሮት የተሞላበት ሰላምታ ለመስጠት እየተዘጋጀው በፈገግታ አዎ ብዬ መለስኩላቸው። ጥያቄያቸው አሁንም አላቆመም “ኤርትራዊ ነህ ኢትዮጵያዊ” አሉኝ እኔም ኢትዮጵያዊ በማለት በአጭር መለስኩላቸው። ሦስተኛውና እጅግ የገረመኝንና ያልጠበኩትን ጥያቄ ቀጠሉ “ምንድነህ አሉኝ” ጥያቄአቸው ግራ አጋባኝና  ጥያቄ በሚመስል አነጋገር አቤት አልኳቸው እርሳቸውም ትግሬ ነህ አማራ ወይስ ኦሮሞ አሉኝ። እጅግ በጣም ደነገጥኩኝ እኔ ከእርሳቸ ስጠብቅ የነበረው ለአገሩና ለከተማው እንግዳ መሆኔን ተረድተው ምን ልርዳህ? ኑሮ እንዴት ነው? የሚል ጥያቄ ስለነበረ የእርሳቸውን ጥያቄ በስዓቱ ለመመለስ ቃላት አጠረኝ። ከብዙ ዝምታ በኋላ “ኢትዮጵያዊ  መሆኔ በቂ አይሆንም” ብዬ ስመልስላቸው በመጀመሪያ ያሳዩኝን ፈገግታ ደግመው ሳያሳዩኝና ሰላም ዋል የሚል የስንብት ድምፅ ሳያሰሙ መንገዳቸውን ቀጠሉ እኔም እዛው ለተወሰነ ጊዜ በሃሳብ ተክዤ ለምን ይህን ጥያቄ ጠየቁኝ ብዬ እራሴን ጠየኩት መልስ ግን ማግኘት አልቻልኩም። አሁን ላይ ግን እርሳቸውንም የዘረኝነቱ መንፈስ በእጅጉ እንደጎዳቸው ተረዳው። እናተ ብትሆኑ ምን ትሏቸው ነበር?
ይህ ነው እንግዲህ የኢትዮጵያ የእድገት ደረጃ፤ ህጻን፣ ወጣት፣ ትልቅ፣ አዛውንት፣ ተማሪ፣ ሙህር ሳይቀር በዘረኝነት መንፈስ መመታት። ታዲያ ይህ ለኢትዮጵ አገራችን ከማነቆም በላይ ማነቆ አይሆንባትም ትላላችሁ? ከወዲሁ መፍትሔ ማፈላለጉ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተረድተን በበሽታው የተጠቁትን ህክምና፤ ያልተጠቁትን ደግሞ  የመከላከል ስራ ለመስራት ቆርጠን መነሳት ይኖርብናል።