Tuesday, September 22, 2015

የሀገር አድን ጥሪ ለወጣቱ!(ከአርበኞች ግንቦት7 ወጣቶች መምርያ )

   
 እኛ የዘመኑ ወጣቶች በሃገራችን ላይ የተጫነብን የወያኔ የመርገምት አገዛዝ ያጎሳቆለን፤ በኑሮ የተበደልንና በሰላም ለመኖር ያልታደልን ፍጡሮች ብንሆንም ህዝባችን ነጻነቱን ሲቀማ፣ መብቱ ሲደፈር፣ ክብሩ ሲዋረድ ከዳር ቁመን የምንመለከትበት አንዳች ምክንያት ሊኖረን አይገባም። ወቅቱ ለነፃነታችንና ለመብታችን ባላንጣ የሆነውን አምባገነን የወያኔን ስርዓት ፊት ለፊት ተጋፍጠን፣ በትግላችን ደቁስን ማንነታችንን የምናስመስክርበት ወቅት እንጂ በፍርሃትና በዝምታ ተውጠን ወደኋላ የምንልበት ስዓት አይደለም። ደግሞም እኛ ወጣቶች ለመብት እና ነፃነታችን ተፈጥሮ የለገሰችንን እምቅ ኃይልና ጉልበት ተጠቅመን በቁርጠኝነት ተነስተን ካልታገልን የሥርዓቱን አምባገነናዊ የጭቆና አገዛዝ በፍርሃትና በዝምታ እንደተቀበልን ተደርጎ መወስዱ የማይቀር ነው።
 ከምንግዜውም በላይ እኛ ወጣቶችን ዛሬ ሁለት አበይት ጉዳዮች በጉልህ ያሳስቡናል፤ ሊያሳስቡንም ይገባል። እነዚህም ሃገራችን ያለችበት አሳሳቢ ሁኔታና የኛ የተተኪው ትውልድ የወደፊት ተስፋ ምን ሊሆን ይችላል? የሚሉት ናችው። በቀደመው ጊዜ በሃገራችን የተፈራረቁት አምባገነን ገዥዎች ለወጣቱ ተስፋና የተሻለ ነገር ከመስጠት ይልቅ በጠላትነት ፈርጀው በሽብር እየገደሉና ጥቃት እየፈጸሙበት ሲያሳድዱት ኖረዋል። የወጣቱ ሰቆቃ አሁን በወያኔ ዘመን ደግሞ እጅግ በጣም በከፋ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል።
 የወያኔ መሪዎች ለኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ማዕከላዊን፡ ቃሊቲን፤ ሽዋሮቢትን፣ ዝዋይን እና የመሳስሉ የሰቆቃ እስር ቤቶችን ሲያሰፉ እንጂ የሥልጠናና የምርምር ተቋም ሲያድሱና ሲገነቡ ለማየት አልታደልንም። የሚገነቡ የትምህርት ተቋማትም ለሥርዓቱ የእድሜ ማራዘሚያ እንጂ የእውቀት ማስጨበጫ ተቋም እንዳልሆኑ ተግባራቸውንና ውጤታቸውን መመልከት ይቻላል። በአደባባይ ያለፍትህ የሚገደለው ወጣት ባንክ ሲዘርፍ ተገኘ፣ ወንጀል ሲሰራ ተያዘ የሚሉ የሀሰት ምክንያቶች እየተለጠፉበት ያለኃጢአቱ የሀሰት ስም በመቀባት ዳግም ይገሉታል።
የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ከሚፈራበት የትምህርት ተቋም ድረስ በመግባት የአማራ ህንጻ፣ የኦሮሞ ህንጻ፣ የትግሬ ህንጻ…ወዘተ እያሉ የትምህርት ሥርዓቱን ከጠባቡ የፓለቲካ ግባቸው ጋር በማያያዝ በነገ ተስፋችን ላይ ዘምተው የልዩነት ግድግዳ ባሳፋሪ መልክ እየገነቡ ቀጥለዋል። አላማው ደግሞ በጎስኝነት በሽታ ተውጠን ከእህቶቻችንና ከወንድሞቻችን ጋር እየተባላንና እየተገዳደልን የምንኖርበት ሲኦል ለመፍጠር መሆኑ አያጠያይቅም። በዚህም ሳቢያ ብሔራዊ ሰሜታችን እየደበዘዘ ሄዷል። ብሔራዊ ሰሜት ከሌለን ደግሞ አገር አለን ማለት ጨርሶ የሚታስብ እንደማይሆን ግልጽ ነው።
 በነገራችን ላይ ዛሬም ድረስ ወያኔዎች ለእድገትና ለልማት መዘጋጀታችውን እየደሰኮሩ ህዝብን በማታለል የስልጣን ዘመናቸውን ለማርዘም መውተርተራቸውን አላቆሙም። በየጊዜው ኢትዮጵያ ተመነደገች፤ ልማቱ ተፋጥኗል እያሉ በሃሰት ህዝብን ለማወናበድ ይሞክራሉ።እውነታው ግን በእጅጉ ተቃራኒ መሆኑን የህዝቡን የኑሮ ሁኔታን በመመልከት መረዳት ይቻላል። ዛሬ የፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝ በፈጠረው የተወሳሰበ ችግር በሀገሪቱ የወጣት ሥራ ፈትና ተጧሪ ሞልቶና ተትረፍርፎ በሚታይበት፤ ሥራ የማግኘት እድል በፓለቲካ ታማኝነት ብቻ በሆነባት ሃገርና ወያኔ የፓለቲካ ሥልጣኑንና ወታደራዊ ኃይሉን ተጠቅሞ የሀገሪቷን ሀብት እያጋበስ በሚዘርፍበት ሁኔታ ላይ ቆመን ልማትና እድገት ማለት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ተራ ማጭበርበሪያና ዲስኩር ካልሆኑ በስተቀር ፈጽሞ ትርጉም የሚሰጥ አይደለም።
ለነገሩ ወያኔ ከመጀመሪያው ጀምሮ ያዘጋጀልን ቃሊቲ፤ ማዕከላዊ፤ ሁርሶን፤ ሽዋሮቢትንና የመሳሰሉትን የማሰቃያ ማጎሪያዎች መሆኑን የተረዳን ስለሆነ በዚህ የምንደናገር አይደለም። ለዚህም ነው በአሁኑ ወቅት እኛ ወጣቶች ተሰባስበንና ተደራጅተን ከመታገል ውጪ ሌላ ምርጫ የለንም ብለን በድፍረት የምንናገረው።
 አምባገነንነት ስርዓት ካልተገታ የአገር ሰላም ሆነ የህዝብ ህልውና እና አንድነት ዋስትና አያገኝም። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሥልጣን የጨበጡት ወንበዴ ግለሰቦች የኢትዮጵያ ህዝብን ሀብት እየተቀራመቱ ለግል ጥቅማቸው የሚያውሉ፣ ህዝቡን የሚገሉ፤ የሚረግጡና የሚበድሉ በተለይ ደግሞ ለባእድ ጥቅም የተገዙ ናቸው። እነዚህ ግለስቦች ብሔራዊ ስሜታችውን አሽቀንጥረው የጣሉ፤ የራሳችውን ባህል፤ ወግ፤ ታሪክና ሕዝብ አምርረው የሚጠሉ ከራሳቸውና ሥልጣን ላይ ካስቀመጧቸው መንግሥታት ጥቅም ውጪ ሌላ ምንም የማይታያቸው ናችው።
ታዲያ የሃገራችን ህልውና ከመቼውም በላይ ለከፋ አደጋ ተጋልጦ ባለበት በአሁኑ ወቅት በተለይ የእኛ የወጣቶች ግዴታና ድርሻ ምን መሆን አለበት ብለን ራሳችንን መጠየቅና ብሎም መልስ ለመስጠት መዘጋጀት ሀገራዊ ግዴታንና ኃላፊነትን ለመወጣት የመጀመሪያው እርምጃ መሆን ይኖርበታል።
ጭቆናንና በደልን በመታገል ረገድ ደግሞ የቀደምት የታላላቅ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን አኩሪ ገድል ለዛሬው ትግላችን ትልቅ የትምህርት ማእከል ሆኖ ያገለግለናል። ሀገራችን ከኋላቀር ሥርዓትና ከብልሹ አገዛዝ ተላቅቃ፤ ድህነትን አሸንቀጥራ ጥላ በልማት ጎዳና እንድትራመድ፤ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን እንዲሆን፤ ማህበራዊ ፍትህ እንዲስፍን ባጠቃላይም ተጨባጭና ዘላቂ ለውጥ በሃገራችን እንዲመጣ ጽኑ እምነት ሰንቀው ለሕዝባዊ ትግሉ ሕይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ሲታገሉ የነበሩ ጀግና ወጣቶች እንዳሉ ታሪክ ያስገነዝበናል።
ዛሬም ጭምር ግንባራችውን ሳያጥፉ መስዋእትነትን በመክፈል እያስመስከሩ ያሉ መኖራቸውን ስንመለከት ጀግና የሚያፈራው ጀግናን ነውና እኛም ወጣቶች አንገታችንን ቀና አድርገን ዛሬም እንደ ትናንቱ ለሃገራችንና ለህዝባችን ነፃነት መታገል ብሔራዊ ግዳጃችን ብቻም ሳይሆን ታላቅ ክብርም ጭምር መሆኑን ተገንዝበን ለሞት ሽረቱ ትግል በቁርጠኝነት መነሳት ይኖርብናል። ከፊታችን ለሚጠብቀንና ሃገራችን እያሰማች ላለው የሀገር አድን ጥሪ መልስ ለመስጠት እኛ የኢትዮጵያ ወጣቶች ከሃገር ቤት እስከ ውጪው አለም ድረስ የተቀናጀና የተቀነባበረ ንቅናቄ በመፍጠር ምላሽ ልንሰጥ ይገባል።
በኅብረትና በጽናት ከታገልን ደግሞ የወያኔን የሰቆቃ አገዛዝ አሰወግደን የሕዝባችንን ሮሮ የማናስቆምበት እና ተጨባጭ ለውጥ በሀገራችን ለማምጣት የማያስችለን አንዳች ምድራዊ ሃይል እንደማይኖር በእርግጠኛነት መናገር ይቻላል። ዛሬ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንዳለ ብልጭ ብልጭ እንደሚል ኮኮብ ብንመስልም በርግጠኝነት ነገ ከፀሐይ ደምቀን ከአሽዋ በርከትን የምንታይበት ጊዜ ይመጣል፤ እየመጣም ነው።
 በመጨረሻም የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ወጣቱን ትውልድ መብቱንና የዜግነት ክብሩን ለመጎናጸፍ እንዲችል ብሎም የሀገር እና የወገን ነፃነትን ለማምጣት ወያኔን ታግሎ ማሸነፍና ከስልጣኑ ማውረድ ግድ ነው ብሎ በጽኑ ያምናል። በአገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም ተበታትኖ የሚገኘውን ወጣት በአገሩ ተከብሮ እንዲኖር የተለየና የተቀደሰ አማራጭ አለው። ይኸውም እየተደራጁ መታገል፣ እየታገሉ መደራጀት ነው ብሎ ንቅናቄያችን ያምናል።
የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የነደፈውን ጊዜ የማይሽረውን ሁለገብ የመታገያ ስልትና አላማን ከግብ ለማድረስ ትግልን በጽናት መቀጠል የሚለው መርሁ ሲሆን ተደራጅቶ በጽናት መታገልን በተግባር ለማዋል ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ወጣት ንቅናቄውን እንዲቀላቀል ጥሪ ያደርጋል። ተደራጅቶ ሊያጠፋን የተነሳን ጠላት በተደራጀ ሃይል ማንበርከክና ከስር መሰረቱ ማስወገድ ይቻላልና። ስለዚህ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በአረመኔው የወያኔ አገዛዝ ላይ የሚካሄደውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል በአገር ውስጥ ወጣቱን በህቡዕ ከማደራጀት ጀምሮ በውጭው ዓለም በየአህጉሩ በተዋቀሩ የንቅናቄው መዋቅሮች አማካኝነት ወጣቱን አደራጅቶ በማንቀሳቀስ አስፈሪ የሆነ የነፃነት ማዕበል ፈጥሯል። አሁንም የንቅናቄውን ዓላማ የሚደግፉና በነፃነት ትግሉ ለመሳተፍ የቆረጡ ወጣቶች እንዲቀላቀሉ የአርበኞች ግንቦት7 ወጣቶች መምርያ በድጋሚ ሃገራዊ ጥሪ ያቀርባል!

ፈሪዎችንና ባንዳዎችን ወደ ጎን በመተው እውነተኛ ታጋዮችን ይዘን ትግላችንን እንቀጥላለን!!!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!  

Thursday, July 9, 2015

Mitsat; የምጻት ቀን ሳይመጣ ከነጻነት ትግሉ ጎን እንሰለፍ!(Yibeltal Gashu)

ይቺ ግጥም በብዙ መከራና  ስቃይ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን መታሰቢያ ትሁንልኝ። የራስችንን ነጻነት በራሳችን ለማወጅ ትግላችንን አጠናክረን ወያኔን ለማሶገድ መረባረብ ይኖርብናል። የምጻት ቀን ሳይመጣ ከነጻነት ትግሉ ጎን እንሰለፍ!

Thursday, June 25, 2015

Philip Hammond warns Ethiopia over treatment of Briton on death row

Foreign secretary condemns detention of Andargachew Tsige in solitary confinement with no access to consular help or right to appeal
 
Placards demand the immediate release of UK citizen Andargachew Tsige, also sometimes spelled Tsege, who was given a death sentence in his absence. Photograph: Alamy
The treatment of a Briton on death row in Ethiopia is threatening to undermine the country’s relationship with the UK, the foreign secretary has warned.
In an unusually blunt statement, Philip Hammond has called for rapid progress in the case of Andargachew Tsige, who is being held in solitary confinement in an unknown location in Ethiopia.
The foreign secretary’s comments, released a year after Tsige was abducted while transiting through Yemen, is a clear sign of official disapproval of the approach taken by the regime in Addis Abbaba. The Foreign Office is escalating the case beyond confidential diplomatic exchanges.
Andy Tsige pictured with his family. Photograph: Yemi Hailemariam/Family

On Wednesday, Hammond spoke to the Ethiopian foreign minister, Tedros Adhanom Ghebreyesus, about the case on the phone. His statement said: “I am deeply concerned that, a year after he was first detained, British national Andargachew Tsige remains in solitary confinement in Ethiopia without a legal process to challenge his detention.
“I am also concerned for his welfare and disappointed that our repeated requests for regular consular access have not been granted, despite promises made.
“I spoke to foreign minister Tedros and made clear that Ethiopia’s failure to grant our repeated and basic requests is not acceptable. I informed Dr Tedros that the lack of progress risks undermining the UK’s much valued bilateral relationship with Ethiopia.

UN investigates Briton on death row in Ethiopia

“I asked Dr Tedros once again to permit immediate regular consular access and for our concerns regarding Mr Tsige’s welfare to be addressed. I have also asked that the Ethiopian authorities facilitate a visit by Mr Tsige’s family. Foreign Office officials will continue to provide consular support both to Mr Tsige and to his family during this difficult time.”
Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, lives in London with their three children. She has spoken to him only once by phone since his abduction.
“He’s in prison but we have no idea where he is being held,” she told the Guardian last month. “He said he was okay, but I’m sure the call was being listened to. He had been in Dubai and was flying on to Eritrea when the plane stopped over in Yemen. He hadn’t even been through immigration. We think Yemeni security took him and handed him over to the Ethiopians.
Yemi Hailemariam outside the Foreign Commonwealth Office in April Photograph: Alamy

“They say there was an extradition agreement, but it was so quick there was no time for any semblance of a legal hearing. Yemen and Ethiopia had close relations then. The [Ethiopian] government have put him on television three times in heavily edited interviews, saying he was revealing secrets.
Advertisement
“He has been kept under artificial light 24 hours a day and no one [other than the UK ambassador] has had access to him.”
Tsige, 60 – known as Andy – had previously been secretary general of Ginbot 7, a political opposition party that called for democracy, free elections and civil rights. He first came to the UK in 1979.
The Ethiopian government has accused him of being a terrorist. In 2009, he was tried with others in his absence and sentenced to death. The latest reports suggest that his health is deteriorating.
His lawyer, Ben Cooper, of Doughty Street Chambers, said: “We welcome the Foreign Secretary condemning the illegality of Andy Tsige’s detention, confirming the fact of his solitary confinement and demanding consular visits. But we have a simple ask: please request Andy Tsige’s return home to his family in London. Mr Tsige was kidnapped by Ethiopia at an international airport and the only remedy for kidnap is release. Why has Mr Hammond not yet asked Ethiopia to release Andy so he can return home to England?”
Juan Méndez, the UN special rapporteur on torture, has written to the Ethiopian and UK governments saying he is investigating Tsige’s treatment.

Who is Andargachew Tsige?
Andargachew, or Andy, Tsige fled Addis Abbaba in the 1970s following threats against his life from the military regime, the Derg, which then controlled Ethiopia.
A student activist, he had attracted the attention of the authorities. His younger brother was killed by the security forces. Tsige escaped into the mountains to join opposition groups.
In 1979, after falling out with fellow rebels, he sought asylum in the UK. He studied at the University of Greenwich and obtained full UK citizenship.
Tsige returned to Ethiopia after the Derg was overthrown but moved back to the UK in the early 1990s where he became active in opposition politics.
In 2005, he returned to Addis Abbaba again. He took part in that year’s election and was briefly imprisoned. after being freed, he founded a new political movement, Ginbot 7, from his exile in London.
The organisation was alleged by the Ethiopian government to have launched a failed coup in 2009. Tsige was condemned to death in his absence.
In June 2014, he had flown to the Gulf to give lectures. An unexpected change to his return route saw him fly back via Yemen where he changed planes. At Sana’a airport, he was arrested by guards and put on a plane to Ethiopia on the grounds that there was an extradition agreement between the two countries.
Supporters say that had he been born white and in the UK, the Foreign Office would have taken a more forceful line in campaigning for his release from death row in east Africa.
His partner, Yemisrach Hailemariam, and their three children live in London. She has campaigned actively for his freedom.
In February a delegation of MPs, led by Jeremy Corbyn, his local member, was scheduled to visit Ethiopia in an attempt to secure his release. The trip was abandoned following a meeting with the Ethiopian ambassador.

Source: Theguardian

Related Articles;

Ethiopia's higher-education boom built on shoddy foundations (Dr Ali Eftekhari)

The country desperately needs new universities to drive development, but most of the 30 built in the last 15 years fall woefully short
 
The declining standard of Nigeria’s premier institution, the University of Ibadan, ten years ago is reflected in Ethiopia where the quality of new universities varies widely. Photograph: George Esiri/REUTERS
Ethiopia’s higher education infrastructure has mushroomed in the last 15 years. But the institutions suffer from curricula being abandonded due to funding cuts, unqualified – but party-loyal – lecturers, and shoddily built institutions. The rapid growth of Ethiopia’s higher education system has come at a cost, but it is moving forward all the same.

Beatings for asking for help: corporal punishment in India's schools
Twenty years ago the Ethiopian government launched a huge and ambitious development strategy that called for “the cultivation of citizens with an all-round education capable of playing a conscious and active role in the economic, social, and political life of the country”. One of the principal results of Ethiopia’s agricultural development-led industrialisation strategy (ADLI) has been a rapid expansion in the country’s higher education system. In 2000 there were just two universities, but since then the country has built 29 more, with plans for another 11 to be completed within two years.
The quality of these new universities varies widely; from thriving research schools, to substandard institutions built to bolster the regime’s power in hostile regions. One professor recalls a hurried evacuation from part of a recently completed university while he was working there: one of the buildings had collapsed.
But there have also been success stories. The University of Jimma, for example, has come first in the Ethiopian Ministry of Education’s rankings for the past five years, and is held up as evidence of ADLI’s efficacy since its establishment in 1999. The most recent development at Jimma, the department of materials science and engineering (MSE), opened for students in 2013, and has quickly expanded to become one of the top research schools in the sub-Saharan region. The department’s founder, Dr Ali Eftekhari, has since been nominated for a fellowship from the African Academy of Sciences on the back of the project’s success.
This success is much-needed. At 8%, African higher education enrolment is significantly lower than the global average of 32%, and Ethiopia trails even further behind, with fewer than 6% of college-age adults at university. Research in science, technology, engineering, and mathematics (Stem) is starting from a particularly low base in Africa. The World Bank reported last year that though the sub-Saharan region has “increased both the quantity and quality of its research” in recent years, much of this improvement is due to international collaboration, and a lack of native Africans is “reducing the economic impact and relevance of research”.
Dr Eftekhari echoes these concerns: “The problem for development in Ethiopia and similar African countries is higher education itself. This is the reason that I focused on PhD programs. “For instance, Jimma’s department of civil engineering has over 3,000 undergraduate students. These civil engineers are the future builders of the country, but there is not one PhD holder among the staff; most only have a BSc.”
Eftekhari improvised and sweet-talked in order to get the department established; in its first year, the department taught 18 PhD students – all native Ethiopians – on almost zero budget, with staff donating their time and money until funding was secured from the ministry of education. Despite the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front’s (EPRDF) push for development, Ethiopia’s political landscape remains a minefield for education professionals, says Eftekhari: “People are always suspicious about the political reasons behind each new project. I decided to start with zero budget to allay those doubts. In developing countries everything has some degree of flexibility. I used this to borrow staff and resources from the rest of the university until we could secure a budget.
“Many of the staff saw the project as a career opportunity,” says Eftekhari, but altruism also played a part. The department’s research focuses primarily on solving the country’s pressing poverty and development problems. “They knew they were actually saving lives,” says Jimma’s innovation coordinator, Maria Shou.
The belief that science and engineering is key to alleviating poverty propels the work of the school. Projects range from the development of super-capacitors for the provision of cheap power, to carbon nanomaterials for Ethiopia’s expanding construction industry. “You only need a couple of weeks in Ethiopia to realise that materials science is a priority,” says Pablo Corrochano, an assistant professor at the school. “Even in the capital you’ll experience cuts in power and water; in rural areas it’s even worse. Producing quality and inexpensive bricks for building houses, designing active water filters, and supplying ‘off-the-grid’ energy systems for rural areas are all vital to the country’s development.”
However, Jimma’s success could be seen as a bit of an anomaly. Paul O’Keeffe, a researcher at La Sapienza University of Rome, who specialises in Ethiopia’s higher education system, believes that similar initiatives are needed, but that the government’s politics are an obstacle: “My research indicates that the rapid expansion of the public university system has seen a dramatic decline in the quality of education offered in recent years. Instead of putting resources into improving the existing system, or establishing a few good institutions, the EPRDF has built many new universities, largely for political reasons.
“A lot of the time the universities are merely shells. They do not function as universities as we would expect and are poorly resourced, and in some cases shoddily built. It would seem that they are built almost as a token where the EPRDF can say to hostile regions ‘look we are doing something for you, we’ve built a university’.”

Ethiopia crackdown on student protests taints higher education success

Even when the universities do function, the quality of education is often low: “Once the funding, say from a western development agency, is finished for a particular course, it is no longer taught as the university authorities believe they can get funding for a new course instead; whatever is the latest fashionable course. So often this type of education for development is not sustainable.”
Reports of spies, classroom propaganda, of curricula that have been abandoned en mass due to funding cuts, and of unqualified staff are common at these universities, which make up the bulk of Ethiopian higher education, says O’Keeffe. “The party line is peddled during class, students are required to join the party, [there are] various reports of spies in the classrooms, who monitor what is said and who says it.”
A lecturer at Addis Ababa University, who wished to remain anonymous, is concerned primarily with the lack of qualifications among staff: “What is disturbing is that those who have just graduated with BAs and MAs are the lecturers. That is the manpower that they have. If you talk with students you wouldn’t believe that these students actually graduated from these so-called universities. Their inability to articulate their thoughts is breathtaking. It is extremely frustrating and you wonder how they have spent four years at university studying a doctorate.”
In this context, the MSE school provides a beacon of hope. The school’s success demonstrates that higher education – Stem research in particular – has the potential to thrive and play a central role in helping Ethiopia to reach its goal of becoming a middle-income nation by 2025, provided political interests are put to one side. Let’s hope the EPRDF takes note.
Source: The guardian , June 22, 2015

Wednesday, June 24, 2015

የአንዱዓለም አራጌ መልክት ከቃሊቲ

ለእያንዳንዳችሁ በተናጠል ልባዊ የአክብሮትና የናፍቆት ሠላምታዬ በግፍ ከታሰርኩባት ጠባቧ ክፍል ይድረሳችሁ!

ኢትዮጵያውያን ለዘመናት እውን ያላደረግነውን የህዝባዊ ልዕልና ጥያቄና ሌሎች ከነፃነት እጦት ጋር የተቆራኙ በአገዛዙ የሚፈፀሙ አያሌ የአፈና ተግባሮችን ለመቃወም በተጠራው በዚህ ሠላማዊ ሠልፍ ላይ ከጎናችሁ መሠለፍ ባለመቻሌ ባዝንም፣ ከተሰለፋችሁላቸው ዓላማዎች አንዱ የእኔና የጓደኞቼን ከእስር መቀቀቅ የሚመለከትና የታሰርኩለትም ዓላማ አካል በመሆኑ በመንፈስ ከጎናችሁ እንዳለሁ አምናለሁ፡፡ በዚህም ታላቅ ደስታ ይሰማኛል፡፡
ኢትዮጵያ ህዝባዊ ልዕልና የሠፈነባት የነፃነትና የዴሞክራሲ ምድር ትሆን ዘንድ የቀደሙ ትውልዶች ከፍተኛ መሰዋእትነት ከፍለዋል፡፡ ሌላውን ትተን የዛሬ 4ዐ ዓመት የተደረገውን ትግል ብቻ መጥቀስ ጥሩ ማሳያ ይሆናል፡፡ የዛሬ 4ዐ ዓመት ‹‹ሕዝባዊ መንግሥት›› ለመመስረት በሚል በተደረገ ትግል ሊለካ የማይችል መስዋዕትነት ተከፍሏል፡፡ ነገር ግን ‹‹ከጎናቸው ተሰልፈን ታገልን የሚሉን ወገኖች ዛሬ የኢትዮጵያን ህዝብ እግረ ከወርች አስረው እየረገጡት ይገኛሉ፡፡
ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሉዓላዊ ሥልጣኑ ባለቤት መሆን አልቻለም፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ ሕዝብ ከገጠር እስከ ከተማ በካድሬዎች ፈርጣማ መዳፍ እየታሸ ነው፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ ከማደናገሪያ ስልትነት ባለፈ የህዝብ የመናገርና የመፃፍ መብት አልተከበረም፡፡ ዛሬም 4ዐ ዓመት በኋላ አገዛዙን የሚቃወሙ ዜጎች በበሬ ወለደ ክስ በግፍ ይታሰራሉ፡፡ እኔና ጓደኞቼ ለዚህ ማሳያዎች ነን፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው ሳይሆን አፈ-ሙዝ ያገነነው በምርጫ ተውኔት 99.6% የህዝብ ድምጽ በመዝረፍ ሀገራችንን በዓለም ፊት የሚያኮስስና የህዝቧን ክብር የሚያዋርድ ተግባር የሚፈፀምባት ሀገር ነች፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ በጥቂት የወቅቱ አምባገነኖች በገዛ ሀገሩ እስረኛ ሆኖ ይገኛል፡፡
ዛሬ እየተካሄደ ያለው ሠልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዘመናት እስራት ነፃ ለመውጣት የሚያደርገው አጠቃላይ ትግል አካል ነው፡፡ ኢትዮጰያውያን የየትኛውም ቋንቋ ተናጋሪዎች ብንሆን፣ የየትኛውም እምነት ተከታዮች ብንሆን፣ የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባሎች ብንሆን፣ በየትኛውም የፆታና የእድሜ ክልል ብንገኝ ሁላችን አንድ የሚያደርግ ሰብአዊ ልዕልናችን ተከብሮ በነፃነት የመኖር ተቀዳሚ አጀንዳ አለን፡፡
ነፃነት ማንም በችሮታ ወይንም በአዋጅ የሚያረጋግጥልን ሳይሆን በነፃነት ለነፃነት የተፈጠርን ሉዓላዊ ፍጡራን መሆናችንን ከልብ ስናምን የምንጎናፀፈው ፀጋ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ትልቁ የነፃነት ጠላት እራስን ዝቅ አድርጎ ከማየት የሚመጣ ፍርሃት ነው፡፡ ፍርሃትን ያላሸነፈ ሕዝብ በአዋጅ ነፃ ሊወጣ አይችልም፡፡ አዋጅ መች ቸገረንና? ፍርሃትን ያላሸነፈ ህዝብ የነፃነቱ ባለቤት ሊሆን አይችልም፡፡ ፍርሃትን ያላሸነፈ ህዝብ ለልጆቹ ነፃ ሀገር ሊያወርስ አይችልም፡፡ የፍርሃትንና የግለኝነት ወረርሽኝ ማስወገድ ፈጽሞ ጊዜ የሚሰጠው ተግባር አይደለም፡፡ ፍርሃትንና ለኔነትን ድልነስታችሁ ዛሬ ለነኀነት መሰለፍ በመቻላችሁ የተግሉን የመጀመሪያና ወሳኝ መዕራፍ ተሻግራችኋል፡፡
ፍርሃትን በማሸነፍ ለነፃነት መታገል ወሳኝ የመሆኑን ያህል፣ ከቀደሙ ስህተቶቻችን መማር፣ ትግሉን በተጠናና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ማካሄድም የዚያኑ ያህል አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡
እስከ አሁን በዝምታችን አምባገነኖች የልብ ልብ እንዲሰማቸው ብሎም አፍነው እንዲገዙን እድል ሰጥተናቸዋል፡፡ እስከ አሁን መብቶቻችንና ሰብአዊ ክብራችን በግደለሽነት እንዲረገጡ በመፍቀዳችን ኢትዮጵያና ሕዝቧ የጥቂት ገዢዎች አንጡራ ሀብት ሆናለች፡፡ እስከ አሁን በቁርጠኝነት ባለመታገላችን ዛሬም እንደ አዲስ ከአምባገነንነት ጋር ግብግብ መግጠም ግድ ሆኖብናል፡፡ የአፈናውን የክፋት ደረጃና የአገዛዙን አሙለጭላጭ የአፈና ስልቶች ግንዛቤ ውስጥ ያስገባና ዘመኑን የሚመጥን የፀና ሠላማዊ ትግል ማድረግ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይጠበቃል፡፡
ሠላማዊ ትግል በአንድ ወይንም በሁለት ሠልፍ የሚቋጭ ሳይሆን አያሌ ስልቶችንና ሠፊና ቀጣይነት ያለውን እንቅስቃሴ የሚያካትት ነው፡፡ የፖለቲካ ባህላችንና አስተሳሰባችንን ከማዘመን ጀምሮ ገዢዎች ነፃነትን የማይፈሩበትን ስነ-ልቦና እንዲላበሱ ማድረግና ለበርካታ ዘመናት በጭቆና ደቅድቅ ጨለማ ውስጥ ያለችውን ሀገራችን የነፃነት ብርሃን ከደር እስከዳር የሚበራባት ሀገር እስክትሆን ድረስ መታገል ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ የላቀና የከበረ ምን ቁም ነገር ይኖራል?
ይህ ትውልድ ለማመን የሚከብዱ ታላላቅ ገድሎችን የሰሩ አባቶች ልጆች መሆናችንን ለአፍታ እንኳ መዘንጋት አይገባውም፡፡ በተግባርም የላቀ ገድል በመስራት ማንነቱን ሊያስመሰክር ይገባል፡፡ አባቶቻችን የሞቱላትንና የአጽማቸው ማረፊያ፣ እትብታችን የተቀበረባትንና የሁለንተናዊ ማንነታችን ማህደርና የልጆቻችን ተስፋና መኖሪያ የሆነችውን የምንወዳትን ሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሰፈነባት የማይደርቅ የህዝባዊ ሉዓላዊነት ምንጭ እስክናደርጋት ድረስ እጅ ለእጅ ተያይዘን ትግላችንን በጽናት መቀጠል የጠበቅብናል፡፡ የዓላማና የህሊና ንጽህናን ተላብሰን ለወንድማማችነት፣ ዴሞክራሲና ነፃነት በምናደርገው ሠላማዊ ትግል ፈጣሪም ከእኛ ጋር እንደሚሆን አምናለሁ፡፡
በመጨረሻም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በእስራኤል አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየከፈልኩት ላለው ዋጋ እውቅና ሰጥተው ስለዘከሩኝ፣ የኢሳት ቴሌቭዥን ተመልካቶችና የዘ-ሀበሻ ድረ-ገጽ ታዳሚዎች ‹‹የዓመቱ ሰው›› ብለው በመምረጠ ላጎናፀፉኝ ትልቅ ክብር ከፍ ያለ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እንዲሁም ሰማያዊ ፓርቲ በግፍ የታሰርን ሰዎች እንድንፈታ በመጠየቁ አመሰግናለሁ፡፡ በአጠቃላይ በፀሎት ከማሰብ ጀምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ከጎኔ በመቆማችሁ የላቀ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡ ይህ የመከራ የሀሩር ወቅት አልፎ ብርሃን በሞላው የፀደይ ወቅት በነፃነት ለመኖር ትግላችንን ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ አጠናክረን ልነቀጥል ይገባልይገባናል፡፡

የኢትዮጵያን ሕዝብም ሆነ ህሊናዩን የሚያሳዝን አንዳችም ነገር ፈጽሜአለሁ ብዬ አላምንም! ፍፁም ሠላም ይሠማኛል፡፡ እኔን እዚህ ያቆመኝ የነፃነት ናፍቆት ነው፡፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!
አንዱዓለም አራጌ (የህሊና እስረኛ

Source: Zehabesha (2013) 

Saturday, June 20, 2015

Ethiopian General Election: An Insult to the People and Democracy (by Graham Peebles)

Every five years the Ethiopian people are invited by the ruling party to take part in a democratic pantomime called ‘General Elections’. Sunday 24th May saw the latest production take to the national stage.
With most opposition party leaders either in prison or abroad, the populace living under a suffocating blanket of fear, and the ruling party having total control over the media, the election result was a foregone conclusion. The European Union, which had observed the 2005 and 2010 elections, refused to send a delegation this time, maintaining their presence would legitimize the farce, and give credibility to the government.
With most ballots counted, the National Election Board of Ethiopia announced the incumbent party to have ‘won’ all “442 seats declared [from a total of 547], leaving the opposition empty-handed…the remaining 105 seats are yet to be announced.” ‘Won’ is not really an accurate description of the election result; as the chairman of the Oromo Federalist Congress, Merera Gudina, put it, this “was not an election, it was an organised armed robbery”.
The days leading up to the election saw a regimented display of state arrogance and paranoia, as the government deployed huge numbers of camouflaged security personnel and tanks onto the streets of Addis Ababa and Bahir Dar. For months beforehand anyone suspected of political dissent had been arrested and imprisoned; fabricated charges drawn up with extreme sentencing for the courts, which operate as an extension of the government, to dutifully enforce.
Despite the ruling party’s claims to the contrary, this was not a democratic election and Ethiopia is not, nor has it ever been, a democracy.
The country is governed by a brutal dictatorship in the form of the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) that has been in power since 1991, when they violently overthrew the repressive Derg regime. The EPRDF speaks generously of democracy and freedom, but they act in violation of democratic principles, trample on universal human rights, ignore international law, and violently control the people.
Independent international bodies and financial donors, from Human Rights Watch and Amnesty International to the European Union and the US State Department, are well aware of the nature and methods of the EPRDF, which is one of the most repressive regimes in Africa. The Committee to Protect Journalists reports that Ethiopia is “the fourth most heavily censored country in the World”, with more journalists forced to leave the country last year than anywhere except Iran.
In the lead up to the recent election, CPJ found that, “the state systematically cracked down on the country’s remaining independent publications through the arrests of journalists and intimidation of printing and distribution companies. Filing lawsuits against editors and forcing publishers to cease production.” Various draconian laws are used to gag the media and stifle dissent, the Anti Terrorist Proclamation being the most common weapon deployed against anyone who dares speak out against the government, which rules through fear, and yet, riddled with guilt as they must surely be, seem themselves fearful.

Democracy and Development

The government proudly talks a great deal about economic development, which it believes to be more important than democracy, human rights and the rule of law, all of which are absent in the country. And, yes, during the past decade the country has seen economic development, with between 4% and 9% (depending on who you believe) GDP growth per annum achieved, the CIA states “through government-led infrastructure expansion and commercial agriculture development.” It is growth, however, that depends, the Oakland Institute make clear, on “state force and the denial of human and civil rights.”
GDP figures are only one indicator of a country’s progress, and a very narrow one at that. The broader Ethiopian picture, beyond the debatable statistics, paints a less rosy image:
Around 50% of Ethiopia’s federal budget is met by various aid packages, totaling $3.5 billion annually. Making it “the world’s second-largest recipient of total external assistance, after Indonesia” (excluding war torn nations, Afghanistan and Iraq), Human Rights Watch states. The country remains 173rd (of 187 countries) in the UN Human Development Index and is one of the poorest nations in the world, with, the CIA says, over 39% of the population living below the low poverty line of $1.25 a day (the World Bank worldwide poverty line is $2 a day) – many Ethiopians question this figure and would put the number in dire need much higher.
Per capita income is among the lowest in the world and less than half the rest of sub-Sahara Africa, averaging, according to the World Bank, “$470 (£287)”. This statistic is also questionable, as Dr. Daniel Teferra (Professor of Economics, Emeritus at Ferris State University,) explains, “In 2008-2011 income per capita (after inflation), was only $131,” contrary to the International Monetary Fund’s (IMF) 2013 report, which put the figure at $320.
The cost of living has risen sharply (current inflation is around 8%) and, as The Guardian reports, “growing economic inequality threatens to undermine the political stability and popular legitimacy that a developmental state acutely needs. Who benefits from economic growth is a much-contested issue in contemporary Ethiopia.” Not amongst the majority of Ethiopians it isn’t: they know very well who the winners are. As ever it is the 1%, who sit in the seats of power, and have the education and the funds to capitalize on foreign investment and development opportunities.
Some of those suffering as a result of the government’s development policies are the 1.5 million threatened with ‘relocation’ as their land is taken – or ‘grabbed’ from them. Leveled and turned into industrial-sized farms by foreign multinationals which grow crops, not for local people, but for consumers in their home countries – India or China for example.
Indigenous people cleared from their land are violently herded into camps under the government’s universally criticised “Villagization” program, which is causing the erosion of ancient lifestyles, “increased food insecurity, destruction of livelihoods, and the loss of cultural heritage”, relates the Oakland Institute. Any resistance is met with a wooden baton or the butt or bullet of a rifle; reports of beatings, torture and rape by security forces are widespread. No compensation is paid to the affected people, who are abandoned in camps with no essential services, such as water, health care and education facilities – all of which are promised by the EPRDF in their hollow development rhetoric.

An Insult to the People

Economic development is not democracy, and whilst development is clearly essential to address the dire levels of poverty in Ethiopia, it needs to be democratic, sustainable development. First and foremost human rights must be observed, and there must be participation, and consultation, which – despite the Prime Minister Hailemariam Desalegn’s duplicitous comments to Al Jazeera that, “we make our people to be part and parcel of all the [developmental] engagements,” – never happens.
The Prime Minister describes Ethiopia as a “fledgling democracy”, and says the government is “on the right track in democratizing the country”. Nonsense. Democracy is rooted in the observation of human rights, freedom of expression, the rule of law and social participation. None of these values are currently to be found in Ethiopia.
Not only is the EPRDF universally denying the people their fundamental human rights, in many areas they are committing acts of state terrorism (one thinks of the abuses taking place in the Ogaden region and the atrocities being committed against the Oromo people, for example, that amount to crimes against humanity.
The recent election was an insult to the people of Ethiopia, who are being intimidated, abused and suppressed by a brutal, arrogant regime that talks the democratic talk, but acts in violation of all democratic ideals.

==============

Graham is Director of The Create Trust, a UK registered charity supporting fundamental social change and the human rights of individuals in acute need. He can be reached at:graham@thecreatetrust.org.

Friday, June 19, 2015

ሰማዕትነት፦ ለዓላማ ሲሉ ማንኛውንም ዋጋ መክፈል መቻል ነው!

ሰማዕትነት ለሰው ልጅ እንግዳ  ነገር አይደለም። የነበረ፣ ያለና የሚኖር ነው። የሰማዕታት ተግባራትና ዓላማቸው የከበረ፣ ስማቸውም ዘላለማዊ በመሆኑ ትውልድና ታሪክ ሲያወሳቸው ይኖራል።
የሰማዕታትን ራዕይ፣ ዓላማና ተልእኮ ፍሬ እንዲያፈራ ማድረግ የትውልድ ታላቅ አደራ ነው።
አደራ መወጣት ከባድ ቢሆንም፤ የሀገር፣ ነጻነት፣ፍትህና ማንነት ብለው ሰማዕትነትን የተቀበሉ ሰማዕታት የሰጡንን አደራ በተገቢው መንገድ ከግብ እናደርሳለን። ራዕያቸውን ሰንቀን ወደፊት ከመጓዝ በቀር ከወያኔ ጋር በምንም በምን አንደራደርም።
ሰሞኑን በአሰቃቂ ሁኔታ በወያኔ አሸባሪ ቡድን በግፍ የተገደለው የህግ ባለሙያ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር፣ የፓርላማ እጩ ተወዳዳሪ፣ የነጻነት ታጋይ፣ ለሀገርና ህዝብ የቆመው ወጣት ሳሙኤል አወቀን እና የአረና ፓርቲ የፓርላማ እጩ ተወዳዳሪ ታደሰ አብርሃን በተመለከተ ዓለም አቀፍ ብዙኃን መገኛዎች በዜናቸው እንዲህ ለታሪክ ዘግበውታል።  

“ከታሰርሁም ህሊናዬ አይታሰርም ከገደሉኝም ትግሌን አደራ በተለይ የኔ ትውልድ አደራ! ተገደልሁም ታሰርሁም ነፃነት አይቀርም!” ሳሙኤል አወቀ

“ማንኛውም የምከፍለው ዋጋ ለሀገሬና ለነጻነት ነው፤ በአካል ብታሰርም ህሌናዬ አይታሰርም፣ ከገደሉኝም ትግሌን አደራ”   ~ በግፍ የተገደለው ሳሙኤል አወቀ

እኛም እንላለን፡፡ አደራህ ከባድ ነው፡፡ ቃልህን እናከብራለን፡፡ አላማህንም እናሳካለን!!!! (ሰማያዊ ፓርቲ)








ሳሚ፦  “ብታሰርም፣ ማንኛውንም ዋጋ ብከፍልም፣ ብገደልም ይህን ሁሉ የማደርገው ለሀገሬና ለነፃነቴ ነው” ያልከው ቃል /ህያው ሆኖ ለዘላለም በክብር በወርቅ ቀልም በልቦቻችን ተጽፎ ከመቃብር በላይ ይኖራል!!!! የሞትክለትን ዓላማ እናሳካለን፤ የአደራ ቃልህን እናከብራለን!!! መሪ ቢታሰርም ቢሞትም ትግል ግን ይቀጥላል . . .እንዲያውም ሚሊዮኖችን የነጻነት ታጋይ ተክቶ ያልፋ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
 ታዴ፦ የሞትክለት የነጻነት ትግል በዓላማህ ጽናት ታድሶ ትውልድ ተረክቦታል! የወያኔ ማፍያ ወሮበላ ቡድን የትግራይን ህዝብ ሊወክል እንደማይችል በግልጽ ለኢትዮጵያ ህዝብ አሳይተሃል!

ክብር ለሰማዕታት! ነጻነትና ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ! ውድቀት ለወያኔ ወሮበላ ቡድን ይሁን!!!


Monday, June 15, 2015

ለእውነት እንዳንታገል አዚም የሆነብን ምንድር ነው?

ስለ እውነት በተግባር እንጂ በቃል ደረጃ ብዙ ማለት ከባድ ቢሆንም ብዙዎች ብዙ ጽፈዋል ተናግረዋል። እውነት ማለት ያዩትን፣ የሰሙትን፣ የሚያውቁ፣ የተረዱትን፣ የሆኑትን እና የሚያምኑበትን ነገር ጨም ቀንሱ በግልም ሆነ በአደባባይ በይፋ መናገርና መመስከር መቻል እንደሆነ የዘርፉ ሙህራን ያስረዳሉ።  በሌላ መልኩ ደግሞ ያላዩትን፣የማያውቁትን፣ ያልሰሙትን፣ ያልሆነን ነገር ሳያረጋግጡ እና የማያምኑበትን ጉዳይ አለመናገር ማለት እንደሆነም አክለው ያስረዳሉ፡፡ በአጭሩ እውነት የሀሰት ተቃራኒ ነው። እውነት ለመናገር፣ ስለ እውነት ለመመስከር በመጀመርያ ሀሰትን መቃወም ይኖርብናል። ስለ እውነት ለመናገር ያልቆሸሸ ንጹህ ሕሊና ሊኖረን ይገባል። ንጹህ ሕሊና እውነተኛ ዳኛ ነውና። ያልተበረዘ፣ያልቆሸሸ እና ንጽህ ሕሊና ሀሰትን የማስተናገድ ባህሪ የለውም።
ሀቀኝነት፣ ታማኝነት፣ እርግጠኛነት፣ ትክክለኛነት፣ ተጠያቂነትን መቀበል እና ሀላፊነትን መወጣት የእውነት መገለጫ ባህሪያት ናቸው። በሌላ አነጋገር እውነት ማለት ጽድቅን ማድረግ፣ መልካም ሥነ ምግባርን መላበስ እና ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ግንባታ መታገል ማለት ነው። እውነት ማለት ሀገር፣ ታሪክ፣ ባህል እና ማንነት ነው። እውነት አድሎ የማይታይበት፣ ርህራሄና ቸርነት በተሞላበት ለሰው ልጅ ሁሉ መልካም ነገር እንዲያገኝ መመኘትና በጎ ተግባራትን ማከናወን ነው። እውነት የሰው ልጅ ዘላቂ ሰላም እና የተረጋጋ ህይወት እንዲያገኝ ከፍተኛ አስትዋጾ ያደርጋል።
ደምት አባቶቻችን  ለእውነት ሲሉ ውድ ህይወታቸውን በሰማዕትነት አሳልፈው ሰጠዋል፤ ብዙ መከራና ስቃይ ተቀብለዋል። ለእውነት ሲሉ ከጊዜያዊ ጥቅም ታቅበዋል። ዛሬም ለእውነት ሲሉ ዋጋ እየከፈሉ የሚገኙ እውነተኛ የእውነት ምስክሮች በብዙ ስቃይና መከራ ውስጥ ይገኛሉ በብዙ ውጣ ውረድ እውነትን መናገር እጅግ መልካምና ልብን የሚያስደስት ቢሆንም እውነትን የሚወዷት ያህል የሚፈሯትና ከቻሉም በሀሰት ለውጠው ለማጥፋት የሚመኙ ብዙዎች ናቸው፡፡ በተለይ ጥቅምና ስልጣን ፈላጊዎች እንዲሁም አምባገነን መሪዎች በዋናነት ለእውነት መጥፋት ዋነኛ ተዋናኞች ናቸው፡፡
አምባገነን መሪዎች እውነትን መከተልም ሆነ መስማት አይፈልጉም። መነሻቸውና ግብራቸው ሀሰት ስለሆነ እውነትን ፈጽመው አያውቋትም። እርግጥ ነው እውነት ለእነሱ ጠላት ናት፤ ታጠፋቸዋለች። እነርሱ የሀገር መጥፋት፣ የታሪክ መዛባት፣ የህዝብ ሰላምና ደህንነት አያስጨንቃቸውም። ለሥልጣን ማራዘሚያ ሀገር ይሸጣሉ፣ ህዝብን ይጨቁናሉ፣ ይገድላሉም።  
በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ስለ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ማውራትና መስበክ ወንጀል ከሆነ ዘመናትን አስቆጥሯል። በዚህ ዙርያም ለምን እና እንዴት ብለው የሚጠይቁ ዜጎች እጣ ፈንታቸው እስር፣ እንግልትና ሞት ሆኗል። በኢትዮጵያም ያለው ይህ እውነትን የሚፈራ እና ከእውነት ፈጽሞ የተጣላ የህወሓት አገዛዝ ለቅ፣ ለእውነት የቆሙትንና ሕዝብ እውነት ያውቅ ዘንድ ያለመታከት እየሰሩ የሚገኙ ጋዜጠኞችን፣ ጦማርያንን፣ የፖለቲካ መሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማሳደድና ማሰ ቀጥሎበታል፡፡ በአጠቃላይ ለነጻነት፣ፍትህና ዲሞክራሲ የሚታገሉ ውድ ኢትዮጵያውያንን  ወያኔ ማንኛውንም ዋጋ ከፍሎ ወደ ግዞት እንዲወረወሩ ማድረግ፣ መግደልና ማሰቃየት የሥርዓቱ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎታል። ወያኔዎች ሰባዊነት የሚባል በውስጣቸው ቅንጣት ስለሌላቸው በነጻነት ታጋይ ኢትዮጵያውያን ላይ የአካልና የሥነ ልቦና አሰቃቂ እና ኢ_ሰባዊ ድርጊት ካለ ምንም ርህራሄ ይፈጽማሉ፤ ዛሬም በመፈጸም ላይ ይገኛሉ።
 የወያኔ ፈላጭ ቆራጭ፣ ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በህብረተሰቡ ላይ የሚያደርሰው ግፍና ሰቆቃ ከመብዛቱ የተነሳ ለእውነት እንዳንቆም እንቅፋት ሆኖብናል። ብዙዎች እውነት መናገር ቢፈልጉም እንዳይናገሩ የተለያዩ አመክንዮ ይሰጣሉ። ከፊሎችም በወያኔ አምባገነን አገዛዝ ተጠልፈው የሥርዓቱ ከዳሚና ደንገጡር በመሆን ከእውነትና ከእራሳቸው ጋር ተጣልተው የሕሊና እስረኞች ሆነው መኖር ጀምረዋል። አብዛኛው ህዝብ ደግሞ  ከእውነት ጋር ለመቆም፣ ለእውነት ለመታገል ጊዜና ወቅት በመጣባበቅ ላይ ይገኛል። ብዙ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የወያኔን የውንብድና አገዛዝ ተቋቁመው ለእውነት ሲሉ ሰማዕትነትን እየተቀበሉ ይገኛሉ። እውነት ዘላለማዊ ሰላም የምታጎናጽፍ ከመሆኗም በላይ ድልን የምታቀናጅ አሸናፊ ናትና።
በዋናነት ለእውነት እንዳንታገል አዚምና እንቅፋት የሆነብን ወሮበላው የወያኔ ቡድን አምባገነናዊ አገዛዝ መሆኑ ግልጽ ቢሆንም በተለያዩ ዘርፈ ብዙ ምክንያቶች ለእውነት እንዳንታገል ሆነናል። እውነትን በቃል ከመግለጽ ባሻገር በተግባር መኖር እንዳንችል ምክንያቶችን በመደርደር ከእውነት ታቅበናል። ለእውነት እንዳንታገል አዚም ከሆኑብን ምክንያቶች መካከል የተወሰኑትን ማንሳት እንችላለን።
Ø  ፍርሃት
 ፍርሃት በአካል እና በሥነ ልቦና እንዲሁም በእለታዊ ኑሮያችን ላይ እንቅፋት ሊፈጥርብን/ሊደርስብን ይችላል ብሎ በማሰብ ከማነኛውም ድርጊት ወይም ማድረግ ካለብን ነገር መቆጠብ/መከልከል ማለት ነው። ፍርሃት ከነጻነትና ፍትህ እጦት የሚመጣ በሽታ ነው። ፍርሃት ቅጣትን ወይም ብቀላን በመፍራት ማድረግ ከምንፈልገው ሁሉ መታቀብ ማለት ነው። ፍርሃት በቡድንም ሆነ በግለሰብ ሊከሰት ይችላል፤ በሀገርና ህዝብ ላይ ግን ሊከሰት አይችልም። ፍርሃት በግለሰብና በቡድን ደረጃ ብቻም ሳይሆን በአምባገነን መንግሥታት ላይም ይከሰታል።  ስልጣንና ገንዘብ በእጅጉ ስለሚፈልጉ ይህንን ሊያሳጣ የሚችል ማንኛውንም ኃይል ይፈራሉ። ስለዚህም ህዝብን በማሰቃየት፣ በማሰርና በመግደል ስልጣናቸውን ያራዝማሉ። ግለሰቦች ይህን መከራና ስቃይ ስለሚፈሩ ለእውነት ከመታገል ወደ ኋላ ይሸሻሉ። ፍርሃት እንደ ህወሓት አምባገነን ገዥዎችን በህዝብ ላይ ስቃይና መከራን የበለጠ እንዲያጸኑ ያደርጋቸዋል፤ ብዕር ይዘው ስለ እውነት የሚታገሉትን፣ ለነጻነት ስርዓቱን የሚቃወሙ የፖለቲካ መሪዎችን፣ ጦማርያንን እና ወጣቱን ትውልድ በአሸባሪነት ተከሰው ግዞት እንዲወርዱ አድርጓቸዋል። የሃይማኖት መሪዎች ሳይቀሩ እውነት ከመናገር ይልቅ ተቋሜ ችግር ሊገጥመው ይችላል በማለት በፍርሃት ተውጠው አምልኮታቸውን እንኳ በስርዓት ማካሄድ እንዳይችሉ አድርጓቸዋል። ስለዚህ ፍርሃት በሁሉም በኩል ለእውነት እንዳንታገል ትልቅ እንቅፋት ሆኖብናል።
Ø  አድርባይነት/ጊዜያዊ ጥቅም መሻት
ለእውነት እንዳንታገል ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል አድርባይነት አንዱ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተዘግቦ እንደምናገኘው ኤሳው ለሆዱ ብሎ በምስር ወጥ ብኩርናውን አሳልፎ ለወንድሙ ለያዕቆብ እንደሸጠው ሁሉ ዛሬም በዚህ ዘመን ለጊዜያዊ ጥቅም ተብሎ ማንነትንና ሕሊናን በመሸጥ ለእውነት ከመቆም ይልቅ አድርባይነትን ተቀብለው ከእውነት ጋር የተጣሉ በርካቶች ናቸው። አድርባይነት ዛሬ የጀመረ ብቻም ሳይሆን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አሉታዊ ተጽኖ ከፈጠሩ ጉዳዮች መካከል ትልቁን ስፍራ ይዞ እናገኘዋለን። በአድርባይነት ታውረው በጣሊያን ወረራ ዘመን መንገድ እየመሩ ወደ መሀል ሀገር ከማስገባት በተጨማሪም የንጉሠ ነገሥቱ የቅርብ ባልሙዋል ከነበሩ መኩዋንንቶች እና መሳፍንቶች መካከል ሳይቀሩ ለጣሊያን ያደሩ ሰዎችን እንደምሳሌ ማንሳት ይቻላል። እነዚህ በአድርባይነት የተጠቁ ወገኖች ወይም ሹማምንቶች ህዝቡ ተቃውሞውን በማቆም መሰሪዋ ጣሊያን ይዛው የመጣችውን የይምሰል እውቀት እና ስልጣኔ በመቅሰም ሀገሩን ያለማ ዘንድ በሀሰት ለመሸንገል ሞክረዋል። መረጃ በመስጠት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ደማቸው በግፍ እንዲፈስ ያደረጉት አድርባዮች/ጥቅመኞች ናቸው። ዛሬም አድርባኞችና ጥቅመኞች ጊዜያዊ ሥልጣንን እና የወያኔን ትርፍራፊ በመልቀም የሀሰት “ልማታዊ መንግስት” የሚል ስም ለጥፈው ሀገርን በመሸጥ፣ ታሪክን በመበረዝ፣ ህዝብን በመበደል፣ በማሰርና በመግደል ዋነኛ ተባባሪዎች እነርሱ ናቸው። ስለዚህ ከአድርባይነት ተላቀን ማንነትንና ሕሊናን በጥቅም ሳንሸጥ እንደ ዜጋ ለሀገር በማሰብ ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ በጽኑ መታገል ይኖርብናል።
Ø  ምን አገባኝነት
እኔ ከሞትኩ ሰርዶ/ግጦሽ አይብቀል እንዳለች አህያ እኔ ከበላሁ፣ ከጠጣሁ፣ ኑሮዬ ከተሟላልኝ ለሌላውና ለሚቀጥለው ትውልድ አይመለከተኝም በማለት ለነጻነት ከሚደረገው እውነተኛ ትግል የሚርቁት ጥቂቶች አይደሉም። የራሳቸው በር እስካልተንኳኳ ድረስ የሌሎች ስቃይ፣ በደል፣ ሰቆቃ፣ እንግልትና ስደት አይመለከተንም በማለት ከሰባዊነት ወጥተው ከዳር የቆሙ በርካቶች ናቸው። ምን አገባኝነት የማንነት፣ ሀገራዊና የነጻነት ጥያቄ እንዳናነሳ እና ሆድ አምላኪዎች በማድረግ ለእውነት እንዳንታገል ያደርጋል።  
Ø  የእውቀት ማነስ
በእውቀት የበለጸገ ትውልድ ሀገርን የመለወጥ አቅም ይኖረዋል። እውቀት ሙሉ ሰው በማድረግ ሀገርን ከማነኛውም አሉታዊ ተጽኖ  በመታደግ ወርቃማ ታሪክ መስራት ይችላል። አባቶቻችን በዚህ ተክህነውበት ነበር፤ ተፈጥሯዊና በልምድ የቀሰሙትን እውቀት ለሀገር ጥቅም በማዋል በተግባር አሳይተዋል። የሀገርን ታሪክ፣ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም የህዝብን ምንነት መረዳትና ጠንቅቆ ማወቅ ሀገራዊ ፍቅር እንዲኖረን ያደርጋል። የበለጸጉ ሀገራት ታሪክንና ብሄራዊ ስሜትን በማስረጽ እያንዳንዱ ትውልድ ለሀገሩ ፖሊስ (እንደ ኢትዮጵያ ፖሊስ ማለቴ አይደለም) እንዲሆን አድርገዋል። ወያኔ ግን ትውልዱ እውቀት አልባ፣ ታሪክ የለሽ ለማድረግ በጎጥና በመንደር ከፋፍሎ ሀገራዊ ስሜት እንዳይኖረው በከፍተኛ ደረጃ እየሰራ ይገኛል። ይህ የእውቀት ማነስ ትውልዱ ሀገራዊ ፍቅር ተላብሶ ለእውነት እንዳንታገል አድርጎናል። ወያኔዎች “በጣሊያን ቅኝ ግዛት በተገዛን ኑሮ” የሚል ትውልድ በማፍራት ሥልጣናቸውን ለማስረዘም እየጣሩ ነው። እውቀታችንን በማዳበር እንደ አባቶቻችን ታሪክ መስራት እንኳ ቢያቅተን ታሪካችንን አስጠብቀን ለተተኪው ትውልድ ማስተላለፍ ሀገራዊ ኃላፊነት አለብን የሚል እምነት አለኝ።
Ø  ተስፋ መቁረጥ
የህግ የበላይነት ባልሰፈነበት፣ አምባገነን መንግሥት በሰለጠነበት፣ ድህነት በተንሰራፋበት ሀገር እውነት መናገርም ሆነ ለነጻነት መታገል ውጤት አይኖርም በሚል ተስፋ የቆረጠ የህብረተሰብ ክፍል በግልጽ ይታያል። ይህ ችግር በተለይ ወጣቱን ትውልድ ለእውነት ከመታገል ይልቅ ስደትን አማራጭ መፍትሄ አድርጎ እንዲጓዝ አድርጎታል። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ዘረኝነት፣ ማን አለብኝነት፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራር በእጅጉ ገዝፎ በመታየቱ ብዙዎችን በቀላሉ የማይቀረፍ ስለሚመስላቸው ተስፋ መቁረጥ ይታይባቸዋል። ተስፋ መቁረት መፍትሄ እንዳልሆነ ቢያውቁትም ለጊዜ ጭቆናን በጸጋ ተቀብለው ሰማያዊ ኃይል በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ብዙዎች ይመስሉኛል። ለውጥ ለማምጣት፣ ተስፍ ለመሰነቅ፣ እውነትን ለማንገስ፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራስን ለማስፈን ችግሮቻችንን ተቋቁሞ ወደፊት መጓዝ ይኖርብናል እንጂ ተስፋ በመቁረጥ ለስደት እና ለባርነት መጋለጥ የለብንም።
በአጭሩ ከላይ የዘረዘርናቸው ምክንያቶች/ችግር ለወሮበላውና ማፍያ ቡድን ወያኔ አሳልፎ በመስጠት ስቃይና መከራ፣ እንግልትና ሰቆቃ፣ እስራትና ግርፋት፣ ሞትና ስቅላት እንድንቀበል አድርጎናል። ብዙኃኑ ህዝብም ይበላው ይጠጣው አጥቶ፣ ነጻነቱን ተገፎ በድህነት ይሰቃያል፤ ለእውነት እንዳንታገል ትልቅ እንቅፋት ሆኖብናል። ታሪክ እንደሚያስረዳን አባቶቻችን ለእውነት ሲሉ ህይወታቸውን አሳልፈው ሰጠዋል። ዛሬም ብዙዎች መከራን እየተቀበሉ ይገኛሉ። እኛም የእነሱን ዓርያ ለመከተል እና ሀገርን ነጻ ለማውጣት የበኩላችንን ድርሻ መወጣት ይኖርብናል። ለእውነትኛ ትግል እንደ መፍትሄ ሊደረጉ ከሚገባቸው ተግባራት መካከል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል።
v  እራስን መሆን/ ለሕሊና መኖር
ማንኛውንም ተግባር ለመፈጸም ቀዳሚው ነገር እራስን መሆን ነው። እራሳችንን በሚገባ ሳናውቅና ሳንረዳ የምናከናውናቸው ነገሮች ዘላቂነት ላይኖራቸው ይችላል። በይምሰልና በሌላ አካል ተጽኖ የምንፈጽማቸው ጉዳዮችም  እንዲሁ ውጤታቸው አያምርም። ስልጣን፣ ገንዘብ፣ ጥቅም ዜያቸውን ጠብቀው ይጠፋሉ። እራስን ለመሆን ሕሊናን ማዳመጥ ይኖርብናል። ሕሊና በእድሜ ዘመናችን ሁሉ እውነተኛ ዳኛ በመሆኑ ትክክለኛ ፍርድ ይሰጣናል፤ ሕሊና ዘላለማዊ ሰላም አልያም ደግሞ ዘላለማዊ ጸጸት ያጎናጽፈናል።  እራችንን መሆን ከቻልን ለእራሳችን፣ ለእውነት፣ ለነጻነት፣ ለፍትህ፣ ለሀገር እና ለወገን መታገል እንችላለን።  እውነተኛ ትግልን ከእራስ እንጀምር፤ ያኔ ለውጥ ማምጣ እንችላለንና።
v  ታሪክን በሚገባ መረዳት
ኢትዮጵያ አኩሪ ታሪክ፣ ባህል እና ኩሩ ህዝብ ያላት ሀገር ናት። የህዝቧ ጀግንነት፣ አይበገሪነት፣ ዳር ድንበር ጠባቂነት እና የጥቁር አፍሪካውያን ተምሳሌነት  በዓለም የተመሰከረላት ብርቅዬ ሀገር ናት። ሀገራችን የመለያየት፣ የሙስና፣ የዘረኝነት እና ተስፋ ያጣ ትውልድ መፍለቂያ አልነበረችም፤ እንደ ሀገር ዛሬም አይደለችም። ይኸን ታሪኳን ብዙ መዛግብት ይመሰክራሉና ማስተባበል አይቻልም። ቀደምት አባቶቻችን የከፈሉት ዋጋ እንዲሁ በታሪክ ሲወሳ ህያው ሆኖ ይኖራል። ታሪካችንን በሚገባ ተገንዝበን እንደ ዜጋ መክፈል የሚገባንን ዋጋ በመክፈል ለእውነት/ለሀገር መቆም አለብን። ታሪክ ሰርተን እንጂ ታሪክ በርዘን ወይም አጥፍተን ለልጆቻችን ማስተላለፍ የለብንም።
v  በእውቀት እራስን ማነጽ
ከላይ እንዳየነው የእውቀት ማነስ ሀገርን ወደኋላ ያስቀራል፤ ማንነትን ያሳጣል፤ ደካማና ፈሪ ያደርጋል። በእውቀት ከታነጽን ግን ለምን፣ እንዴት እና መቼ እንደምንታገል በደንብ ተረድተን ከዓላማችን እንደርሳለን። እውቀት በዓላማና በስልት እንድንታገል ይረዳናል። ነጻነት፣ፍትህ፣ ዲሞክራሲ እና ልማት ምን ማለት እንደሆነ እንረዳለን። እውቀት ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ለይቶ ያወጣል። እውቀት ወያኔ እንደሚያወራው ህንጻ መገንባት፣ መንገድ መስራት፣ ግድብ መገደብ፣ የሀገሪቱን ለም መሬት ለውጭ ባለሃብቶች ማቀራመት፣ ህዝብ ሃብት ንብረት አፍርቶ ከሚኖርበት ማፍለስ እና ወዘተ የዘላቂ ልማት መገለጫ እንዳልሆነ እንድንረዳ ያደርጋል። እውቀት ከምንም በላይ ለሰባዊ መብት፣ ለነጻነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ እንድንቆም እና በጽኑ እንድንታገል ከፍተኛ አስተዋጾ አለው። ስለዚህ በእውቀት መታነጽ ያስፈልጋል።
v  አንድነትን መፍጠር
ስለ አንድነት ብዙ መተንተን አስፈላጊ መስሎ አልታየኝም፤ በተግባር እንጂ በቃላት የሚገለጽ አይደለም። አባቶቻችን በተግባር አሳይተውናልና። በእውነት ወያኔን ከህዝብ ጫንቃ ላይ አሶግዶ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለመገንባት ከሆነ የማስመሰል ሳይሆን እውነተኛ ህብረት/አንድነት ይኑረን። በዘር፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት ተለያይተን ለውጥ ማምጣት በፍጹ የማይታሰብ ነው። “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንደሚባለው ተባብረን በአንድ ላይ ከቆምን እንኳን ወያኔን ጣሊያንን ድባቅ የመቱ ኢትዮጵያውያን አርበኞች ልጆች ነንና ጊዜ ሳይፈጅብን ሀገራችንን ነጻ ማውጣት እንችላለን።  ስለዚህ አንድነት ይኑረንና ከዘረኛው ወያኔ እራሳችንና ሀገራችንን ነጻ እናውጣ!
በአጠቃላይ ለእውነት እንዳንታገል አዚም የሆነብንን ነገር አሶግደን ከእኛ የሚጠበቀውንና ጊዜው የሚጠይቀውን ማንኛውንም ዋጋ በመክፈል ለእውነት ከቆሙ እና ከነጻነትና ፍትህ ታጋዮች ጋር በመቀላቀል በይፋ እውነትን መስበክ ሀገራዊ ግዴታ አድርገን እንነሳ። እኛ በውጭም በውስጥም የምንኖር ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያን የወያኔ ተራ የሃሰት ወሬና ማስፈራሪያ ሳይገድበን ለነጻነትና ፍትህ በጽናት እንታገል። ለእውነት፣ ለሀገር፣ ለነጻነትና ፍትህ ብለው ስቃይና መከራ፣ እስራትና ግርፋት እንዲሁም ሞት የተፈረደባቸውን እውነተኛ ታጋዮችን በማሰብ  የእነርሱን ራዕይ እና ሀገራዊ ተልእኮ ከግብ ለማድረስ እኛ ለእውነትና ለእውነት ብቻ በመታገል ሀገርራችንን ከወያኔ ዘረኛና አምባገንን አገዛዝ እንታደግ።

ለእውነትና ለእውነት ብቻ እንታገል! አዚም የሆነብንን ወያኔን በነገር ሁሉ እንቃወም!!!

Thursday, May 21, 2015

የእኛ ዝምታ ለወያኔዎች?

እኛ ኢትዮጵያውያን ዝምታ ወርቅ ነው እየተባልን ማደጋችን የጠቀመንን ያክል ጉዳቱም በዚያው ልክ ከፍተኛ ሆኗል። እውነት ነው በዝምታ ውስጥ ትዕግስት ፣ ማስተዋልና አርቆ አሳቢነት ይንጸባረቅበታል። ይህንን የማይረዱ አካላት ግን ፍርሃት ወይም ድንቁርና ይመስላቸውና ሰባዊና ዲሞክራሲያዊ መብታችንን ይገፋሉ፣ ይነጥቃሉ፣ ይጨቁናሉም። ሁልጊዜም በዝምታ ውስጥ እንድንኖር ይመክራሉ፣ ያበረታታሉ፣  ያስፈራራሉም። ዛሬ የመገናኛ ብዙኃን በረቀቀበትና በተስፋፋበት ዘመን ያለውን እውነታ ግን በሚገባ እናውቃለን። ነገር ግን እውነትን በውስጣችን አፍነን መናገር እየቻልን እንዳንናገር፣ መስራት እየቻልን እንዳንሰራ፣ ለውጥ ማምጣት እየቻልን እንዳንለወጥ፣ ነጻነትና ዲሞክራሲን መጎናጸፍ እየቻልን የነጻነት እጦት እያሰቃየን ለዘመናት በአምባገነን ስርዓት ተጉዘናል። ከመቼውም በበለጠ ደግሞ ዛሬ ላይ ችግሩ ገዝፎና እጥፍ ድርብ ሁኖ ለብዙ ወገኖቻችን የስደትና እስራት ምክንያት ሁኗል።
እርግጥ ነው ዝምታን ሰብረው ስለ ነጻነት ብዙ የተናገሩ፣ የጻፉ እና በአደባባይ የመሰከሩ ሰዎች እጣ ፈንታቸው ወደ እስር ቤት ተወርውረው የህሌና እስረኞች ሆነው ወርቃማ ጊዜያቸውን የአለግባብ እንዲያሳልፉ መደረጉ ይታወቃል። ለእነዚህም እውነተኛ ኢትዮጵያውያን ስቃይና መከራ መብዛት አይነተኛ ምክንያት የእኛ የብዙዎቻችን ዝምታ መጨመሩ ነው። ምንም በደል ሳይገኝባቸው በሀገራቸው አረመኔያዊ ቡድን ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡ፣ ሲንገላቱ፣ ውድ ህይወታቸው በከንቱ ሲሰዋ እያየንና እየሰማን “ነግ በእኔ” የሚለውን እረስተን በዝምታ ቁመን እንመለከታለን። ብዙዎቻችንም ችግሩን የግለሰብ ወይም የፖለቲካ ድርጅቶች ወይም ደግሞ  የሰባዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ብቻ እናደርገዋለን።
ምስጋና አይድረሳቸውና ወያኔዎች “እኩልነትን” በተግባር የሚያሳዩበት ትልቁ ተቋም እስር ቤት ነው። ማንኛውም ስርዓቱን የሚቃዎምም ሆነ ግላዊ አስተያየት ሰጪ ሴት፣ ወንድ፣ ወጣት፣ ጎልማሳ፣ አዛውንት ሳይባል ሁሉም በእኩልነት ስቃይ፣ መከራና እስራት ይጠብቀዋል።ከመተቸት/ ከመቃወም እራሱን እስካልገታ ድረስ የወያኔ የማሰቃያ ቦታዎች በራችውን ከፍተው ዘወትር ይጠባበቃሉ። ወገኖቻችን ለነጻነት ብለው ሲታገሉ፣ ለዲሞክራሲ ብለው ሲደሙ፣ ለእኩልነት ብለው ህይወታቸውን አሳልፈው ሲሰጡ እኛ በምን አገባኝነት ቁመን እናያለን። ይህን እኩይ ተግባር ለማስቆም ህዝብ እንደ ህዝብ በአንድነት ከመናገር ይልቅ ዝምታን ስለመረጠ ለወያኔዎች ጋሻና መከታ ሆኗቸዋል።
ወያኔዎች ለሥልጣን ማራዘሚያ አይነተኛ መሳርያ አድርገው የሚጠቀሙበት የህዝብን ዝምታ ነው። ጸሎት አይሉት ድሎት ህዝብ በአርምሞ ውስጥ ”ተመሰገን ማለት ነው የባሰ እንዳይመጣ መጸለይ ነው“ እያለ እንዲኖር በተለይ የወያኔ ተላላኪ የሀይማኖት መሪዎች ሳይቀሩ ህዝብን ለዝምታ ይገፋፋሉ። ወያኔወችም ዝምታን ለማስፈን በአጽንኦት ይሰራሉ፤ ተሳክቶላቸዋል ማለትም ይቻላል። ወያኔዎች ለክፋትና ለተንኮል፣ ሀገርን ለማጥፋት ህዝብን ለመበደል ያእቀዱትን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ የሚደርስባቸው የለም። ምክንያቱም ሰውን ለመግደልም ሆነ ለማሰቃየት ምንም አይነት ሰባዊ ርህራሄ የሚባል ነገር በውስጣቸው የለምና።
መቼም በዚህ በአለንበት በሰለጠነው ዘመን የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ይበጃል፣ ይጠቅማል፣ ይመጥናል የሚል ህሊና ያለው እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብሎ መገመት ያዳግታል። ሥርዓቱ ከአምባገነናዊነት ባሻገር ብሄራዊ ቀውስ እና የሀገርርን ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ፣ የብዙ ንጹኃንን ደም ያፈሰሰ፣ ብዙዎችን ለስደትና እስራት የዳረገ አረመኔያዊ አገዛዝ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃም ይህ የወያኔ እኩይ ተግባር የተገለጠና የተመሰከረለት ነው። ለዚህም መረጃም ማስረጃም እኛው እራሳችን ነን። በዝምታ ውስጥ የማንኖር እና እንደ ሀገር የምናስብ ከሆነ በቀጥታ ማስፈራርያ፣ ዘለፋ፣ እስራትና እንግልት በወያኔዎችና ተላላኪዎች ደርሶብናል፤ እየደረሰብንም እንገኛለን። ነገር ግን ይህ ገደብ የለሽ ማስፈራርያ ለዝምታችን ምክንያት መሆን የለበትም፤ ይልቁንም ለመብት፣ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ እንድንነሳ ግፊት ያደርጋል እንጂ። እውነት ነው ፍርሃት እስኪመስል ድረስ ዝምታችን በእጅጉ በዝቷል፤ የዝምታችንም ውጤት ለወያኔወች አረመኔያዊ ኃይል እንዲያገኙ እና በወገኖቻችን ላይ ሰይጣናዊ ድርጊት እንዲፈጽሙ፣ ጥጋብንና ማንአለብኝነትን እንዲላበሱ እድል ፈጥሮላቸዋል።
እንደሚታወቀው በየአምስት ዓመቱ የይስሙላና የቅርጫ ምርጫ በደረሰ ጊዜ ለሀገርና ለወገን ዴንታ የሌለውን ጥቅመኛ ቡድን ፍትሃዊ ምርጫ ለማስመሰል መራጭ በማድረግ አብዛኛውን ህብረተሰብ ደግሞ በዝምታ እንዲያሳልፍ ይደረጋል። ይህ ሥርዓት ለሀገር የሚበጅ ሥርዓት አይደለምና ይወገድ ብሎ እንዳይናገር “ብንናገር እናልቃለን” የሚለውን የሞኝ ፈሊጥ እንዲያስተጋባ የዝምታ ካባ ይደረብለታል። ምርጫው እንደሆነ የተበላ እቁብ መሆኑ ዓለም በሙሉ ያውቀዋል። በወያኔ “በጎ ፈቃድ” በምርጫ እንዲሳተፉ የተደረጉት ተቀዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችም ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ ለማስመሰል ቅመም ወይም ቅባት እንጂ ወያኔ በስልጣን ላይ እያለ መቀመጫ ወንበር አግኝተው ፓርላማውን እንዲቀላቀሉ አይደለም። ውይይት፣ ትችት፣ ማካፈልና አብሮ  መስራት የወያኔ ባህሪ አይደለም። 24 ዓመታት የወያኔን ስርዓት በሚገባ አይተናል፤ ባህሪውንም ተረድተናል። “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” እንዳለች አህያ ህዝብና ሀገር ለማጥፋት በአህያ አስተሳሰባቸው ተግተው እየሰሩ ነው።
የተባበሩት የዓለም መንግስታት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ዲሞክራሲን የሚናፍቁ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ግለሰቦች የኢትዮጵያ ምርጫ የይስሙላና ኢ-ፍትሃዊ እንደሆነ ከአለፉት ምርጫዎች ስላረጋገጡ ከመታዘብ እራሳቸውን አቅበዋል። እውነት ነው ለውጥ ለማይመጣ ነገር ገንዘብ፣ ጉልበትና ጊዜ ማቃጠሉ ከንቱ ነው። እኛም በምርጫ ለውጥ እንደማይመጣ በሚገባ እናውቃለን፤ ግን ዝምታችን እስከ መቼ ይዘልቃል በዝምታስ ለውጥ ማምጣት ይቻላልን በዝምታ ለውጥ ያመጣ ሀገር በታሪክ አጋጣሚ ተዘግቦ አላየንም። እውነት እላችኋለው “እውነትን እውነት፡ ሀሰትን ሀሰት” እስካላልን ድረስ ለውጥ ሊመጣ በፍጹም አይችልም። ነጻነትን፣ ፍትህንና ለውጥን እኛ እናመጣዋለን እንጂ እራሱ በር አንኳኩቶ ሊመጣ አይችልም።
ጭቆናው ጨምሯል ሰው በሰውነቱ፣ በኢትዮጵያውነቱ፣ በተግባሩና በሥራው ሳይሆን በማንነቱ፣ በሚናገረው ቋንቋ፣ በተወለደበት አካባቢ ስም  እየወጣለት ለስቃይና ለመከራ ይዳረጋል። የሥጋ ቆጠራ ይመስል የዘር ግንዱ እየተመዘዘ፣ የተጸውዖ ስም ሳይቀር እየታየ አድሎ ይደረግበታል። ወያኔን የሚቃረን የፖለቲካ አመለካከት ማንጸባረቅ እንኳ የማይታሰብ ነው። ወያኔዎች የጸረ ሽብር ህጉን ተፈጻሚ የሚያደርጉት በእንዲህ አይነት ሰዎች ላይ ነው። ይህን እያየንም፣ እያወቅንም ዝምታ
ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማርያን፣ የሰባዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ተማሪዎች፣ ነጋዴዎች፣ አርሶ አደሮችና አያሌ ንጹሃን ዜጎች በግፍ ሲታሰሩ፣ ሲሰደዱና ሲገደሉ በዝምታ ከመመልከት በላይ ምን የከፋ ነገር ይኖራል። ፈሪ የሚል ቅጽል ስም ቢወጣልንም ስህተት ነው የማለት የሞራል ድፍረት አይኖረንም። አዎ ብዙዎች በግፍ ሲታሰሩና ሲሰደዱ በዝምታ ተመልክተናል፤ ዛሬም ሰማያዊ ወይም ምዕራባዊ ኃይል እየጠበቅን ይሆን እንጇ ቁመን እያየን ነው። ለውጥ ለሌለው የይስሙላ ምርጫ ጆሮአችንን ሰጠን የወያኔን ተራ የሀሰት ወሬ በዝምታ ውስጥ ሆነን እየሰማን እንገኛለን።
በአጠቃላይ የእኛ ዝምታ ለወያኔች መከታ፣ ስልጣን ማራዘሚያ፣ ሃብት ማካበቻ፣ ድንቁርና፣ ማንአለብኝነት ማጎልበቻ ሲሆናቸው ለሀገራችን ኢትዮጵያ ድህነት፣ ኋላ ቀርነት፣ ለውጭ ዜጎች ገነት ለልጆቿ ሲዎል እንድትሆን ሲያደርጋት ለእኛ ለህዝቧ ደግሞ እስራት፣ ስደት፣ እንግልት፣ መከራ፣ የነጻነትና ፍትህ እጦት፣ የመብት ጥሰት እና ውርደትን እንድናስተናግድ አድርጎናል። እኛ በሌሎች ሀገሮችም ሳይቀር እንደ ሰው እንዳንታይ እና ክብር እንድናጣ ዝምታችን አሉታዊ አስተዋጾ አድርጓል።
ስለዚህ ዝምታን በመስበር “የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውን እንመሰክራለን” እንዲሉ ለሀገር የማይጠቅም ለህዝብ የማይሆን ይህን አረመኔያዊ የወያኔ አገዛዝ ከስር መሰረቱ ማስወገድ ጊዜ የማይሰጠው የቀን ተቀንና የዕለት ተግባር ማድረግ ይገባናል። ሀገር ለባዕድ ስትሸጥ፣ ህዝብ በድህነት ሲሰቃይ፣ ብዙዎች በግፍ ሲሰደዱ፣ ሲታሰሩና ሲገደሉ እያዩ  እንዳላዩ፣ እየሰሙ እንዳልሰሙ መሆን የታሪክ ተወቃሽ ያደርጋልና ዝምታ ይብቃ። ሌባን ሌባ ለማለት እንደምንደፍር ሁሉ ወያኔንም የሌቦች፣ የቀማኞችና የወንበደኞች አለቃ ነውና በቃ ከህዝብ ጫንቃ ላይ ውረድ ማለትን እንድፈር።
 ካለመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል እንደሚባለው ዝምታን አስወግደው ለነጻነትና ለፍትህ የሚናገሩ ብዙ ኢትዮጵያውያን በተለያየ ቦታ ዝምታ ይብቃ እያሉን ነው። በእስር ቤት ሆነውም ሀገራዊ መንፈሳቸው ነጻነት ነጻነት ነጻነት እያለ በአደባባይ ይሰብካል። እውነተኛ ኢትዮጵያዊ አንደበታቸው ወያኔን ያሸብራል።  ሰውን ያክል ክቡር ፍጡር በእስር እያሰቃዩ  ፍትሃዊ ምርጫ እያሉ ማውራት አግባብ እንዳልሆነ በዝዋይ፣ በቃሊቲ፣ በቂሊንጦ፣ በማዕከላዊ፣ በሽዋ ሮቢት እና በሁሉም የማሰቃያ እስር ቤቶች የሚገኙ ውድ ኢትዮጵያውያን ድምጻቸው ያስተጋባል። ለይስሙላ ምርጫ ከመሰለፍ ይልቅ ለነጻነት ተሰለፉ ይሉናል።
ለነጻነትና ለዲሞክራሲ ግንባታ በርሃ ወርደው ብረት አንግበው የሚታገሉ ወገኖቻችን ኑ በህብረት ወያኔን እናስወግድ፤ ጉልበት ያለህ በጉልበት፣ እውቀት ያለህ በእውቀት፣ ገንዘብ ያለህ በገንዘብ ተደጋግፈን ለተከበረች ኢትዮጵያ እንድረስላት በማለት ሀገራዊ ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ነገር ግን በያለንበት ወያኔን ማሳደድና ማዋከብ ከቻልን ሁላችንም በርሃ መውረድ ላይጠበቅብን ይችላል። በተለይ እኛ ወጣቶችጉልበታችንን፣ ኃይላችንንና አቅማችንን ተጠቅመን ወያኔን የምናስወግድበትን ስልት በመንደፍ ከሁልጊዜ ስቃይና መከራ ለተወሰነ ጊዜ ትግል ማድረጉ በእጅጉ የተሻለ ነውና በህብረትና በአንድነት ሀገር የማዳንን ትግል እንቀላቀል። በሀገር ተከብሮና ተዝናንቶ መኖር ሲቻል ስደትን አማራጭ መንገድ በማድረግ ለባህር ቀለብ፣ ለአሸባሪዎች የትንሳኤ በግ፣ ለአረብ የጥጋብ ማስታገሻ መሆን የለብንም። በአጠቃላይ ዝምታን በማስወገድ ህዝብን በማስተባበር ነጻነትን ለማወጅ ቆርጠን እንነሳ እላለሁ።

ዝምታ ይብቃና የወያኔን የይስሙላ ምርጫ በመቃወም ነጻነታችንን ለመጎናጸፍ አማራጭ መንገዶችን እንጠቀም!!!

Saturday, April 25, 2015

“የምንታረድበት ቀን ደርሷል፣ ጓደኞቻችን ታረዱ፤ እኛም አሁን ተራችንን እየጠበቅን ነው”

ሰሞኑን በሊቢያ በኢትዮጵያኖች ላይ የደረሰው አረመኔያዊ ድርጊት ሁላችንንም መሪር ሃዘን ውስጥ ከቶናል። እንቅልፍ ነስቶናል። መደበኛ ስራችንን ሳይቀር ማከናወን ተስኖናል። ምክንያቱም ድርጊቱ በሰው ልጅ ላይ ሊደረግ ቀርቶ የማይታሰብ ሰይጣናዊ ድርጊት ነውና። በህይወት የሚገኙትን ከዚህ አሸባሪ ሰይጣናዊ ቡድን ማዳን አለመቻላችን ደግሞ ሃዘናችንን እጥፍ ድርብ አድርጎብናል። በሰማዕትነት ላለፉት ክርስቲያን ወንድሞቻችን አንብተናል፣ አልቅሰናል፣ ውስጣችን ደምቷል፤ እኛም እንደ እነሱ በመንፈስ ታርደናል።
ብዙዎች በተለያየ መልኩ ሐዘናቸውን እየገለጹ ነው። ለዚህ ያበቃንን መንግስት ነኝ ባዩን በመኮነን ላይም እንገኛለን። ለብዙዎች የስደት ዋናው ምክንያት የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ መሆኑ የታወቀና የተረጋገጠ ነው። በመተባበር ለአገርና ለህዝብ ጠላት የሆነውን ወያኔን ማሶገድ  ዘላቂ መፍትሄ ሊሆን እንደሚገባም ብዙዎቻችን እንስማማለን።
እስከዛው ግን በስቃይና በመከራ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንን በሚቻለው ሁሉ መታደግ አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው ብዬ አምናለሁ።
ዛሬ በቅርብ ከማውቀው ሰው ከሊቢያ በቫይበር መልእክት ደረሰኝ። ስደውልለት ማናገር እንደማይችል መልእክት ላከልኝ።  ፎቶግራፉን ሲልክልኝ ማመን አቃተኝ። እጅግ በጣም ተጎሳቁሏል፣ የሐዘን ስሜት ይነበብበታል። እኔም የት እንዳለ እና በምን ሁኔታ እንደሚገኝ ጠየኩት። ተስፋ በቆርጠ አነጋገር “የምንታረድበት ቀን ደርሷል፣ ጓደኞቻችን ታረዱ፤ እኛም አሁን ተራችንን እየጠበቅን ነው” አለኝ። እጅግ ከባድና አስቸጋሪ ነው ማጽናናት እንኳ የማይቻልበት ወቅት። እኔም ግራ ገባኝ እንደማነኛውም ሰው ሐዘን ተሰማኝ ይበልጥ ደግሞ  ምንም ማድረግ አለመቻሌን ሳስበው።
37 ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠባብ ቤት በሊቢያ እና ሱዳን ጠረፍ ደንጉላ በምትባል ስፍራ ታስረው እንዳሉ ገለጸልኝ። ሊወጡ የሚችሉበት መንገድ  እንዳለም ጠየኩት፤ ለእያንዳንዳችን 2000 የሱዳን ገንዘብ መክፈል ከተቻለ የመለቀቅ እድል እንዳላቸው ነገረኝ። ያን መክፈል ካልተቻለ ግን ለአይ ኤስ አይ ኤስISIS) አሳልፈው እንደሚሰጧቸው አስረዳኝ። ብዙ ኢትዮጵያውያን ጓደኞቻቸው በዚህ መልኩ እንዳለቁ ነገረኝ። እንዴትና በምን መልኩ ገንዘብ ሊደርሳቸው እንደሚችል ጠየኩት፤ ሱዳን በሚገኝ ደላላ አማካኝነት ለአሳሪዎቹ ገንዘቡ ሊደርሳቸው ይችላል አለኝ። የደላላይ ስልክም ተቀብዬ ደጋግሜ  ብደውልም ላገኘው  አልቻልኩም። አማራጭ ስልክ እንዲሰጠኝ በጠየኩት መሰረት በደላላው የቅርብ ጓደኛ ደጋግሜ ደውዬ ሳናግረው ገንዘብ መክፈል ከተቻለ እንዲለቀቁ እና ወደ ሱዳን እንዲመለሱ  ማድረግ እንደሚቻል አረጋገጠልኝ።
ይህን መረጃ ለኢሳት ለማስተላለፍ ወደ ዲሲ ስቲዲዮ ደጋግሜ ደወልኩ ግን የስራ ቀን ባለመሆኑ ስልኩ ሊነሳልኝ አልቻለም። አሁን ብቸኛ አማራጭ ሁኖ  ያገኘሁት ይህን መረጃ በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ለወገን ደራሽ ወገን ነውና ለኢትዮጵያውያን ማድረስ  ነው።
ውድ ኢትዮጵያውያን፦ በሰማዕትነት የተሰውትን ነፍሳቸውን በክብር ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን እኛንም አምላከ ቅዱሳን መጽናናቱን ይስጠን ከማለት ውጭ ምንም ማድረግ አንችልም። ስለዚህ በሞትና በህይወት መካከል በብዙ ስቃይና መከራ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንን በሚቻለን አቅም እንድረስላቸው። የሰው ደም ከጠማው አረመኔና ጨካኝ አይ ኤስ አይ ኤስ አሸባሪ ቡድን እንታደጋቸው። ቢያንስ አንድ ንጹህ  ሰው ማትረፍ ለህሌናችን ትልቅ እረፍት እናገኛለን።
ወገኖቼ ምን እናድርግ??? እርዳታችንን በግል ከምናደርገው በህብረትና በመመካከር ቢሆን ብዙ ነፍስ ማድን እንችላለን በማለት ወደ እናንተ  ማድረሱን ወደድኩ።
አስፈላጊ መረጃዎቹንስልክ ቁጥሮችንእርዳታ ለማድረግ ለሚፈልግ ሁሉ እሰጣለሁ።  ለቤተሰብ እና ለአንዳንድ ጥንቃቄዎች ሲባል ስልክ ቁጥርና ፎቶ ግራፉን እዚህ ላይ ከማውጣት ተቆጥቢያለሁ።

ይበልጣል 

Friday, March 27, 2015

Nile Dam Tripartite Agreement: who loses and who benefits? Why we should not celebrate too soon

by Aklog Birara (DR)

አምላካችን ያበረከተላትን ይህን ኃብቷን (አባይን) ለሕዝቦቻቸው ሕይወትና ደህንነት በማዋል እንዲጠቀሙበት ከጎረቤት ወዳጂ አገሮች ጋር በለጋስነት በጋራ ለመካፈል ዝግጁ ብትሆንም፤ ይህን የውሃ ንብረቷን በቁጥር እየጨመረ ለሚሄደው ሕዝቧና በማደግ ላይ ላለው ኢኮኖሚ ጥቅም እንዲውል ማድረግ የኢትዮጵያ ተቀዳሚና የተቀደሰ ግዴታዋ ነው።
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፤ ጥቅምት 1957 ዓም
Watercourse States shall in their respective territories utilize an international watercourse in an equitable and reasonable manner. In particular, an international watercourse shall be used and developed by watercourse States with a view to attaining optimal and sustainable utilization thereof and benefits there from, taking into account the interests of the watercourse States concerned, consistent with adequate protection of the watercourse.
Convention on the Law of the Non-navigational Uses of International Watercourses, UN General Assembly resolution 49/52 of December 1994
I read the full text of Principles Al-Ahram (the Nile dam agreement), Egypt’s leading newspaper posted on the Nile Dam Agreement. The Agreement is a celebration for Egypt but of questionable efficacy for Ethiopia. This historic document was arrived at after a series of consultations at the highest levels of government and State on the Egyptian side; and signed on March 23, 2015 by Prime Minister Hailemariam Dessalegn of Ethiopia, former Field Marshall turned President Abdel Fattah Al-Sisi of Egypt and President Omar Hassan Ahmed al-Bashir of Sudan.
Nile Dam Tripartite Agreement
The Abbay River is dear to me and to millions of Ethiopians. In light of this, I had written a series of papers under the title ዐባይ እንደ ዋዛ in favor of Ethiopia’s fundamental rights to harness its water resources for the benefit of its own people; and urging Egypt to stop its belligerent, hostile, militaristic and bellicose approach in dealing with Ethiopia and other Sub-Saharan Africa riparian states. I had urged Egypt to rejoin the Nile Basin Initiative (NBI) that it abandoned for five years. Refusal resulted in the unintended consequence of cementing relations among Black African riparian states. Sudan moved out Egypt’s spell and Egypt stood alone.
After listening to the Egyptian position and strategy of scuttling any form of “hydropower hegemony in Africa”—a clear reference to the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) —in Doha, Qatar, I came to the conclusion that Egypt would do everything in its power to preserve its colonial based agreement of “historic and natural rights.” The question in my mind was what tactic it would deploy to achieve this? Finance opposition groups as it has done in the past? Use military force as the former President of Egypt Morsi had indicated? Accept the dramatic geopolitical and economic forces that are transforming Sub-Saharan Africa and creating new alliances in place of old ones? Opt for diplomatic solutions by restoring normal relations with Sub-Saharan African countries, including its primary traditional adversary, Ethiopia?
We now know the answer. For the first time in decades Egypt faces enormous challenges within and without. Renewed interest in Sub-Saharan Africa and more willingness to use diplomacy in protecting its national security interests reflects dramatic changes in the Arab world, the fragility of the country and the unease in the body politic within Egypt, and economic transformation in Sub-Saharan Africa. Equally, the government led by Prime Minister Hailemariam Dessalegn faces enormous political and economic challenges. Part of this challenge is perceived military threat from Egypt, internal political tensions and shortage of foreign exchange. In one of my articles on the subject, I had said the following concerning Morsi’s military solution. “Experts agree that his short-lived Presidency was well known for its frightening extremism calling for military intervention in Ethiopia and Syria. It seems to me that, in the long-run, Ethiopia and Egypt would benefit more from cooperation than confrontation. However, given the current turmoil in Egypt and continued repression in Ethiopia, no one really knows how the contentious issue of the Nile would end. One question to ponder is the extent to which the Egyptian military establishment’s position is radically different from that of President Morsi and the Muslim Brotherhood?”
It is reasonable to entertain the notion that the former Field Marshall decided to opt for diplomacy by giving a little, recognition of the GERD.
Egypt’s Diplomatic Coup
The “good news” is that Egypt has rejoined the Nile Basin Initiative (NBI). Second, Egypt has been forced to acknowledge Ethiopia’s right to build the GERD. In principle, The Nile Basin Cooperative Framework Agreement that the Ethiopian Parliament ratified in 2013 replaces the 1929 Colonial Agreement that gave Egypt and Sudan the lion’s share of Nile waters. So, in this sense history is on Ethiopia’s side. In theory, Egypt is in no position to impose all sorts of conditions on Ethiopia if it accepts the Framework; and unless the Ethiopian government falters for its own reasons. A cursory review of negotiations and studies by Egyptian experts since 2011 shows that Egypt was determined not to give an inch with regard to water flows; and, as an insurance policy, decided to have a say in the administration and monitoring of the GERD itself. Article 5 of the Agreement gives Egypt a window of opportunity to have a say in Ethiopia’s project. “The principle of the Dam’s storage reservoir first filling, and dam operation policies,” binds signatories “To apply the recommendations of the international technical experts committee and the results of the final report of the Tripartite National Technical Committee during different stages of the dam project.” It further confirms “The three countries should cooperate to use the final findings in the studies recommended by the Tripartite National Committee and international technical experts to reach:
a) An Agreement on the guidelines for different scenarios of the first filling of the GERD reservoir in parallel with the construction of the dam.
b) An agreement on the guidelines and annual operation policies of the Renaissance Dam, which the owners can adjust from time to time.
c) To inform downstream countries, Egypt and Sudan, on any urgent circumstances that would call for a change in the operations of the Dam, in order to ensure coordination with downstream countries’ water reservoirs.
–Accordingly, the three countries are to establish a proper mechanism through their ministries of water and irrigation.
–The timeframe for such points mentioned above is 15 months from the start of preparing two studies about the dam by the international technical committee.
My reading is that Egypt and Sudan will be in a position to exercise substantial right in the “filling of the reservoir” and the “operational policies” of the Dam. Is this not a surrender of Ethiopia’s sovereignty and national security to Egypt? What is the difference between the Colonial period protocol of giving veto power to Egypt and this Agreement? Is this not ceding Ethiopia’s sovereignty over a national project housed on Ethiopian territory and river over which Ethiopia should be the only power that dictates the construction and operation of its own dam as long as it is done in a responsible manner? Doesn’t Egyptian absolute oversight and interference in Ethiopia’s internal development administration reaffirm Egyptian claim of “historic and natural rights” over the Abbay River? What happens in the event that water flow to Egypt decreases during different stages of the “first filling of the GERD?” Does the Agreement not offer a free hand to Egypt to demand that Ethiopia stops building the dam? I am not an expert on the technicalities of the Dam. Nevertheless, this Agreement compromises Ethiopia’s national sovereignty, national security and long term interests. Its sets the worst precedent possible for the country.
There are additional points. How do we reconcile equitable rights with an Agreement that is patently unfair and unjust? It will be inconceivable for Ethiopia or any other Sub-Saharan African riparian state to exercise oversight in the administration of the Aswan Dam or the construction of future dams by Egypt or Sudan. As far as I can tell from the document Prime Minister Hailemariam signed on behalf of Ethiopia there is no quid pro quo.
Principle 5 diminishes the value contained in 9. “The principle of the sovereignty, unity and territorial integrity of the State” offers a consolation prize. It states “The three countries cooperate on the basis of equal sovereignty, unity and territorial integrity of the state, mutual benefit and good will, in order to reach the better use and protection of River Nile.” An Agreement that is patently unequal among the three countries cannot, at the same time, engender “equal sovereignty.” In my estimation, it is clear that if this Agreement is ratified by Ethiopia’s single party dominated Parliament, Ethiopia will be at a huge disadvantage for decades to come.
President Sisi made a brilliant move when he addressed the Ethiopian Parliament commending the Ethiopian government for its understanding, flexibility and seeking good will in support of Egypt’s water needs. He acknowledged Ethiopia’s right to build the GERD. From this, let us accept his recognition as “victory” for the Ethiopian government and its supporters” during an election year with a foregone conclusion that the ruling party would win. This “victory” does not diminish the fact that Egypt has attained a diplomatic coup that will affect Ethiopia’s sovereignty, national security and economic interests for decades to come. What Egypt has failed to achieve by military means or through surrogates, the Egyptian President played the diplomatic and public relations game superbly and preserved his country’s security and economic interests. Principle 5 discussed above is illustrative of this coup.
Ethiopia does not do well with regard to other binding principles either. The first principle agreed is that there will be a binding “cooperation in understanding the water needs of upstream and downstream countries across all their lands.” At face value this is fair as long as each country has the right to use its waters for its own development even if it means that there will be some decrease in water flows to Egypt. Is this a trick? For example, will Ethiopia be in a position to build dams for irrigation purposes in accordance with this principle? We do not know. This concern is expressed more fully in Principle 3, “Principle of not causing significant damage.” It says that “The three countries will take all necessary procedures to avoid causing significant damage while using the Blue Nile (Abbay…In case significant damage is caused to one of these countries, the country causing the damage is to take all the necessary procedures to alleviate this damage and discuss compensation whenever convenient.” Just think of this. Both Egypt and Sudan have established enormous irrigated-agriculture employing millions of people and producing food. Egypt not only produces some of its food supplies; it produces the finest cotton on the planet, a gift from Ethiopia. It has built state of the art textile factories that produce garments and other products for the domestic and global market. Ethiopia is no position to dictate to these countries that irrigated farming is water intensive and that, this tradition is no longer sustainable. The greater concern I express is that Ethiopia’s right to use the GERD for some irrigation is not allowed. Further, this precedent might offer Egypt a legal agreement in preventing Ethiopia to build irrigation dams.
What do I conclude?
Two policy issues in the Agreement distress me most. First, the total abandonment of Ethiopia’s sovereignty with regard to the construction, fill of the water reservoir and operation of the GERD whose construction I supported from its inception with substantial critique on ownership and social value added. Second, the fact that Ethiopia is disallowed to use any portion of the waters from the GERD and other future dams for irrigation. The Ethiopian government signed an Agreement that says in effect the following. It is acceptable for Ethiopia to produce hydro power for export but illegal for Ethiopia to use its waters for irrigation. It is acceptable for Ethiopia to build the GERD as long as Egypt exercises overwhelming oversight. I ask myself “How does the Ethiopian government justify binding itself and future governments and generations from managing its own epic hydroelectric power project without interference by Egypt and experts that Egypt approves; and from using waters within Ethiopia’s own boundaries for irrigation that would meet the food requirements of 100 million Ethiopians and growing? This is patently unfair, unjust and unacceptable.
President Sisi signed the Agreement after thorough review of the Principles and substantial consultation with Egyptian experts. His decision was backed by enormous amounts of rigorous research and recommendations. Upon closer reading, I find interesting similarities between elements of the Agreement and Egyptian expert recommendations. I wonder if the same rigor occurred in support of the Ethiopian side. I do not know.
I recall a group called the Group of the Nile Basin (GNB) “composed of Professors from Engineering, Irrigation and Hydraulics” who took matters to the next level. Their ultimate objective was to “support the effort of the Egyptian Government and decision-makers” through scientific research, scenarios and policy options. Their studies showed that Ethiopia’s four large dam projects including the Renaissance Dam posed threats to Egypt’s security. They accused the Ethiopian government of failure “to conduct “sufficient structural and hydrologic studies and environmental assessments.” These experts agreed that the Egyptian government should try to adhere to Agreements of 1929 and 1959 in any negotiation. They concluded, “Reduction in the water share of Egypt will result in abandoning huge areas of agricultural lands and scattering millions of families. It would result in in increasing the pollution of the water streams and creating problems in the supply of water for drinking and industry.” They offered the following recommendations to the Egyptian government thereby undermining Ethiopia’s national interests in advance of the Agreement.
  • “Request stopping the construction of the Dam until completion of negotiations
  • Insist that the maximum size of the Ethiopian Dam must not exceed 14 billion cubic meter compared to the 74 billion cubic meter” designed and under construction by Ethiopia
  • Insist that Ethiopia commit officially not to use the water behind the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) for irrigated agriculture
  • Insist that Ethiopia commit to give advance notice of future projects it has in mind
  • Insist that the design and modification of the GERD be reviewed by Egyptian and international experts
  • Insist that Ethiopia’s Dam must be used solely for electric power generation and never for irrigation
  • Negotiate so that the price of electricity sold to Egypt and Sudan would be at cost thereby nullifying the value added from the project and negating the market itself
  • Insist that filling the waters of the Dam’s reservoir should be staggered over 6 years to reduce disruption to Egypt’s supply and
  • Insist that the operation of the hydro plant should be coordinated with Egypt,” thereby undermining Ethiopia’s sovereignty and diminishing its power.
We therefore knew well in advance that these recommendation offered by Egyptian experts were incongruent with a rising and assertive Sub-Saharan Africa of which Ethiopia is a part. These lop-sided solutions undermine the entire intent of the GERD and Ethiopia’s sovereign right to harness its waters without undue influence and pressure from Egypt or other third parties. Egyptian experts had told the Ethiopian government repeatedly that nothing of substance that will affect the flow of water from the Blue Nile to Egypt would be allowed through negotiation either.
President Sisi went to Ethiopia and lived up to the standard of successive Egyptian governments that their primary responsibility is to defend this sacred water—the source of life—by any means necessary. The Ethiopian people have the right to know specifics of the deal.

Related Articles: