Showing posts with label Politics. Show all posts
Showing posts with label Politics. Show all posts

Monday, September 30, 2013

400,000 ብር እና አዲስ ፕሬዝዳንት

በአዲስ ዓመት እንደ አገርም እንደ ግለሰብም አዲስ ሥራ ለመሥራት ይታቀዳል። በዚህ አመት ደግሞ ልዩ የሚያደርገው አገራችን ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንታዊ "ምርጫ" (ምርጫ የሚለውን ቃል የተጠቀምኩት ሕገ መንግሥቱን ለማክበር እንደ ሆነ ይታወቅልኝ) የምታካሂድበት ጊዜ መሆኑ ነው። መንግሥት (አገራችን ብሎ ለመናገር አስቸጋሪ ስለሚሆን ነው) በሕገ መንግሥቱ መሰረት በየስድስት ዓመቱ የአዲስ ፕሬዝዳንት ምርጫ ያካሂዳል። በዚህ አመትም ክቡር ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የ12 አመት የፕሬዝዳትነት ስልጣናቸውን የሚለቁበት ጊዜ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ 2 አነጋጋሪ ጉዳዮች ጎልተው ወጥተዋል።

1. ቀጣይ አገሪቱን በፕሬዝዳትነት ማን ይምራት

 ለአገራችን እድገትና ሰላም የሚያስቡና የሚቆረቆሩ ምሁራን በተለያየ መልኩ አገሪቱን ማን ቢመራት የተሻለ ሊሆን ይችላል ብለው ሃሳባቸውን በማካፈል ላይ ይገኛሉ። ከእነዚህም መካከል በኖርዎይ ኦስሎ, ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሴር ተክሉ አባተ በጡመራ ድረ ገጻቸው ላይ ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል።

በአንድም በሌላም አገራችንን የተሻለ ሰው ቢመራት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ምኞት ነው። ነገር ግን ማነው የተሻለውን ሰው በፕሬዝዳንትነት ቦታ ላይ እንዲቀመጥ ማድረግ የሚችል የሚለው ትልቁ ጥያቄ ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ መቀመጥ ቢችልስ አቅሙንና እውቀቱን ተጠቅሞ መስራት የሚችልበት ከባቢያዊ አየር አለ ወይ ነው። በግልጽ ቋንቋ መንግሥት እንዲህ አይነት ሰዎችን ይፈልጋል ወይ የሚለው የሁላችንም ገሃዳዊ ጥያቃችን ነው።

ስለ አዲስ ፕሬዝዳንት ስናነሳ በስፖርቱ አለም ታዋቂነትን ያተረፈውና አገራችን ኢትዮጵያን ለአለም ስሟን ያስተዋወቀው አንበሳው ኃይሌ ገ/ስላሴ በምርጫው እንደሚሳተፍ የተገለጸበት ሌላው ትልቁ ወቅታዊ ጉዳይ ነው።



ኃይሌ ገ/ስላሴ Google pic

ኃይሌ ገ/ስላሴ በህብረተሰቡ በኩል ትልቅ ቦታና ክብር ያለው ሰው እንደ መሆኑ መጠን በዚህ ምርጫ የሚሳተፍ ከሆነ ብዙ ነገሮችን መመልከትና መወሰን ይኖርበታል።

  1. የመንግሥትንና የህብረተሰቡን የአንድነት ሁኔታ
  2. የመንግሥትን ምንነት(እውቀቱንና ስልጣኑን በነጻነት መጠቀም መቻሉን)
  3. በመንግሥትና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ያለውን ልዩነት
  4. በመንግሥትና ውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውን መካከል ያለውን ልዩነት
  5. ለቀጣይ 6 ወይም 12 አመት አገሪቱን በፕሬዝዳትነት ለመምራት የሚያስችል በቂ እውቀት መኖሩን ...ወዘተ
ወደ ምርጫ ከመግባቱ በፊት እነዚህንና መሰል ነገሮችን በሚገባ ማጤን ይኖርበታል። ነገሮችን ሳይመለከት ቢገባ ግን ክብሩንና የወደፊት ጉዞውን በቀላሉ ሊያጣ እንደሚችል መገመት አያዳግትም። ምክንያቱም የአገራችን መንግሥት በህብረተሰቡ ዘንድ በተለያየ መልኩ ተቀባይነቱ በእጅጉ የቀነሰበት ሁኔታ ላይ በመሆኑ የኃይሌንም የወደፊት ጉዞ አስቸጋሪ እንዳያደርግበት የብዙዎች ሃሳብ ነው።

2. የክቡር ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የወደፊት የኑሮ ሁኔታ




የክቡር ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የወደፊት ሕይወት ነው። ከኃላፊነት የተነሱት የአገርና የመንግሥት መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የምክር ቤት አባላትና ዳኞች የሚያገኙዋቸውን መብቶችና ጥቅሞች ለመወሰን መንግሥት ባወጣው አዋጅ መሰረት ለተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ቤት በወር 400,000 ብር መከራየቱን ጠቅሳል፡፡ ይህ ከፍተኛ የቤት ኪራይ ወጪ ግን ከአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ሲገናዘብ ለማመንና ለመቀበል አስቸጋሪ ነው። እኔ ግን ትልቅ ጥያቄ የፈጠረብኝ መንግሥት ለፕሬዝዳንቱ የተከራየው ቤት መኖርያ ወይስ የንግድ የሚለው ነውና ደሞዛቸውስ ስንት ነበር የሚለው ነው። መኖርያ ቤት እንደሆነ ደግሞ ተገልጾልናል፤ ነገር ግን መኖርያ ቤት ይህን ያክል ወጪ እንዴት ሊያወጣ ቻለ የሚለው የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ስለዚህ አገሪቱ ለአንድ ከኃላፊነት ለለቀቀ ባለስልጣን ለቤት ኪራይ፣ ለመኪና፣ ለሰራተኛ፣ለህክምና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞችን ጨምሮ ከፍተኛ ገንዘብ በወር ወጪ ታደርጋለች ማለት ነው። ይህን ጉዳይ መንግሥት ለአገራችን በምን ያክል መጠን እንደሚያስብ በጥልቀት ለመረዳት በጎ አጋጣሚ ፈጥሮልናል።
በዚህ ዙርያ የእኔ ሃሳብ ይህን ያክል የአገሪቱን ገንዘብ ወጪ ከማድረግ ይልቅ መንግሥት ከኃላፊነት ለሚለቁ ከፍተኛ ኃላፊዎች የሚሆን ቤት ቢያስገነባ የተሻለ ይሆናል። ምክንያቱም የሚገነባዉ ቤት ለወደፊት የአገሪቱ ቋሚ ንብረት ይሆናል፤ ከዚያም በላይ ለኪራይ በየወሩ የሚወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ይቀንሳል።



Tuesday, September 3, 2013

የሃማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አስፈላጊ ነበር???

ይህ ጉባኤ በዋናነት የተቋቋመው ለአገር ሰላምና በእምነት ተቋማቸው ለሚያስተዳድሩት ህብረተሰብ(የእምነት ተቋም) ደህንነት እንጂ ለመንግሥት ወይም ለአንድ የፖለቲካ ድርጅት አይደለም። በተለይ ደግሞ ይህ ጉባኤ በእምነት ተቋማት መካከል አለመግባባት እንዳይፈጠር እና ወደ አልተፈለገ ግጭት/እሰጣ ገባ/ ውስጥ እንዳይገባ ሁሉም የየራሱን የሃይማኖት አስተምሮ በመቻቻል እንዲሁም ሰላምና ፍቅር በተሞላበት መንገድ እንዲያካሂዱ ለማድረግ የተቋቋመ ይመስለኛል።
በትናትናው እሁድ ማለትም በ26/12/2005 ዓም የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ግን ከዓላማው በእጅጉ የራቀ እና ሁኔታዎችን ያላገናዘበ መስሎ ይታያል። እርግጥ ነው ይህ ጉባኤ አገራዊ ሰላም ሊያደፈርሱ ይችላሉ ብሎ ያመነባቸውን ጉዳዮች ለህዝብ ይፋ ማድረጉ የሚበረታታና ለወደፊትም ሊቀጠልበት የሚገባ ተግባር ነው። ነገር ግን ይፋ ከማድረጉ በፊት የሃይማኖት ኮሚቴ እንደመሆኑ መጠን በርካታ ቅድመ ስራዎች ሊኖሩት ይገባል። የህብረተሰቡን ነባራዊ ሁኔታ፣ የእምነት ተቋማት አመለካከትና የፖለቲካ አቅጣጫን በሚገባ ማጤን ከዚህ ትልቅ ከሚቴ ቀርቶ ከአንድ ግለሰብ ሊሰወር የማይገባ ነገር ነው።
የህብረተሰቡን ነባራዊ ሁኔታ በትክክል መገንዘብ ያስፈልጋል ሲባል የተፈጠረውን ችግር ህብረተሰቡ በምን መልኩ ነው የተረዳዉ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያስወጣ በሚችል መልኩ ነው? ውይስ የግንዛቤ እጥረት አለበት? ወይስ በሌላ አቅጣጫ ነው የተረዳው? የሰላማዊ ሰልፍ አስፈላጊነት? እና መሰል ጥያቄዎችን በማንሳት ህብረተሰቡ ያላበትን የግንዛቤ ደረጃ መለካት፣ ማጤንና መመልከት ይገባል። እንዲሁም ህብረተሰቡን ግንዛቤ ከማስጨበጥ አንጻርም ይህ ኮሚቴ ትልቅ ኃላፊነት አለበት። ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ውሳኔ ከመወሰኑ በፊት የችግሩን አሳሳቢነት ማለትም በአገርና በሃይማኖት ተቋማት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ችግር በሚገባ በተለያየ መልኩ ማስረዳትና ማሳወቅ፣ መግለጽና ማስተላለፍ ይኖርበታል። ምናልባት ኮሚቴው ይህን አድርጊያለሁ ቢልም በቂ ነው ብዬ አላምንም። በዚህ መልኩ ህብረተሰቡን ማንቃትና ወደ አንድ የግንዛቤ መንፈስ እንዲመጣ ሳያደርጉ ውሳኔ መወሰን ይባስ ብሎ አገራዊ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራት ከጥቅሙ ጉዳቱ እጅግ የከፋ ይሆናል።
የእምነት ተቋማት አመለካከት ምን ይመስላል የሚለውንም በሚገባ መረዳት የኮሚቴው ተቀዳሚ ተግባር ነው። የዚህን ኮሚቴ የእያንዳንዱ አባል የወከለው የእምነት ተቋሙ ነው። ስለዚህ ከእምነት ተቋሙ ጋር መነጋገር፣ መወያየት፣ የችግሩን አመጣጥና ሁኔታ፣ በተቋሙ ላይ ሊያስከትለው የሚችለውን ችግር በሚገባ ማየትና ተደጋጋሚ ውይይቶች ያስፈልጋሉ። ችግሩ ተፈጠረ ከተባለበት ተቋም ወይም ቦታ ድረስ በመሄድ ችግሩን በውውይት ለመፍታት መሞከር ይኖርበታል። በእኔ አመለካከት የሃይማኖት ተቋማት ከመንግሥትም በላይ ለሰላምና ለህብረተሰቡ ደህንነት የሚቆሙ ናቸው። ስለዚህ ችግሩን በውይይት፣ በትምህርትና በተግሳጽ ለመፍታት መጣር ያስፈልጋል። ኮሚቴው እንደኮሚቴ ከመወሰኑ በፊት ከወከለው የእምነት ተቋም ጋር ግልጽ ውይይት አድርጎ ችግሩን ሊፈታ በሚችል መልኩ አንድ አቋም መያዝ ይኖርበታል። በእውነት የትናቱ ሰላማዊ ሰልፍ ግን የተፈጠረውን ችግር ሊፈታ ይችል ነበር??? መልሱን ለእናንተ ትቸዋለሁ።
ይህ ኮሚቴ ከፖለቲካ ነጻ እንደመሆኑ መጠን / በወረቀት ደረጃ ማለቴ ነው/ አንድ ውሳኔ በሚወስንበት ጊዜ የፖለቲካ አቅጣጫውን መመልከት ያስፈልገዋል። ምንም እንኳ ሃይማኖትና መንግሥት የተለያዩ ናቸው ቢባልም መንግሥት ከሃይማኖት ነጻ ሁኖ ስለማያውቅ አቅጣጫውን እና ሂደቱን ከውሳኔ በፊት መረጃዎችን መሰብሰብና መፈተሽ ያስፈልጋል። የህብረተሰቡ የፖለቲካ አመለካከት ምን ይመስላል? የገዢው ፓርቲ ያለበት ደረጃ? የተቀዋሚ የፖለቲካ እንቅስቃሴና ሌሎችንም ተያያዝ ነገሮችን መፈተሽ ይኖርበታል። እነዚህ ሁኔታወችን ሳይገነዘብ ወደ ውሳኔ ከገባ ግን በአንድ ተጽዕኖ ውስጥ ሊገባ ይችላል፤ ይኸው ገባም። የሃይማኖት ተቋም የሰላም ኮሚቴ ተብሎ በአንድ ተጽዕኖ ውስጥ ዥው ብሎ መግባት ግን ችግሩ እንዲበባስ ያደርገዋል፤ በተጫማሪም ሌላ ችግር ይፈጥራል እንጂ መፍትሔ ሊያመጣ አይችልም።
ጉባኤው መመልከት ያልቻላቸው ግልጽ ነገሮች፦
1. ችግሩን፦ ጉባኤው በአዲስ አበባ በ10 ክፍለ ከተሞችና በ116 ወረዳዎች በተካሄደው ህዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ እንዲሁም ከፍትህ ቢሮ ጋር በመተባበር ከነሐሴ 15-16 በተካሄደው የሰላም ኮንፈረንስ ላይ የሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮቻቸው «ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማችን እየታየ ያለው የአክራሪነትና የፅንፈኝነት እንቅስቃሴ የሀገራችንን ሰላምና ልማት የሚያውክ፣ በሰላም አብሮ የመኖር እሴቶቻችንን የሚያናጋና የሃይማኖት መልክ የሌለው የጥፋት እንቅስቃሴ ከመሆኑም በላይ በህገ መንግሥታችን የተደነገገውን የሃይማኖት እኩልነትና የእምነት ነፃነት የሚፃረር ስለሆነ በሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሟችንን ማሰማት እንፈልጋለን» ተብሎ በአቋም መግለጫ የተላለፈውን መሰረት በማድረግ ሰልፉ እንደተዘጋጀ በጋዜጣዊ መግለጫ ስለሰልፉ አስፈላጊነትም በማብራራት ሰላማዊ ሰልፉ በመጪው እሁድ ከንጋቱ 12 ሰዓት በመስቀል አደባባይ የሚካሄድ ሲሆን፤ በከተማው ውስጥ ያሉ የሃይማኖት ተቋማት በሙሉ በጋራ በመሆን ለሰላም፣ ለልማት፣ ለመቻቻልና ለአብሮነት ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚገልጹበት የሰላም መድረክ ነው//፤ በማለት የጉባኤው ኮሚቴ በገለጸልን መልኩ ችግሩን ሙሉ በሙሉ እንውሰደው ብንል እንኳ የሃይማኖት አክራሪነት ከመቼ ወዲህ ነው በሰላማዊ ሰልፍ ሊገታ የሚችለው። ኃያላን አገራት እንኳ በተደራጀና ዘመናዊ ስልትን በመጠቀም አክራሪነትን ማቆም ሳይችሉ እኛ እንዴት ነው በሰላማዊ ሰልፍ ልናቆመው የምንችለው። እንደ አገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ሰላማዊ ሰልፍ ለሰላማዊ ትግልም ልንጠቀምበት አልታደልንም። ስለዚህ ጉባኤው የሃይማኖት አክራሪነትን በሰላማዊ ሰልፍ ለመግታት መሞከሩ የችግሩን ምንነት አለመረዳት ነው። ችግሩን በሚገባ ሳይረዱ ደግሞ ውሳኔ መወሰኑ ከመፍትሔው ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ብዙ መናገር የሚያስፈልግ አይመስለኝም። ችግሩም መቶ ፐርሰንት/100%/ አክራሪነት ነው ብሎ ለመፈረጅ ማስረጃ የሚያጥር ይመስለኛል። በግሌ አክራሪነት የለም፣ አይኖርም የሚል አመለካከትና ግንዛቤ የለኝም። ቢሆንም ግን በሰላማዊ ሰልፍ ከችግሩ እንወጣለን የሚል እምነት ፍጽሞ አይኖረኝም።
2. ስዓት፦ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲጀመር የተደረገበትን ስዓት እንኳን ስንመለከተው ጉባኤው ከወከለዉ የእምነት ተቋም ጋር ጥብቅ ውይይት አለማድረጉን በቀላሉ መመልከት እንችላለን። በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን እና ሌሎችም ማለት ይቻላል በየሳምንቱ እሁድ ጥዋት የአምልኮት ስርዓታቸውን የሚፈጽሙበት ስዓት ነው። ስለዚህ ስዓቱን እንኳ ያገናዘበ ሰላማዊ ሰልፍ አለመጥራት የግደለሽነት ያስመስላል። ወይም በሌላ ተጽዕኖ ውስጥ መሆኑን በግልጽ ለመረዳት አያዳግትም። በተጽዕኖዎችና በግደለሽነት የሚደረጉ ማንኛውም ነገሮች ደግሞ ችግርፈጣሪ እንጂ ችግር ፈቺ መቸውንም አይሆኑም።
3. ቀን፦ በሰላማዊ ሰልፉ አስፈላጊነት ጉባኤው ካመነ በቀላሉ ሊመለከተው የሚገባው ነገር የሚደረግበትን ቀን ነው። በዚያ ቀን ምን ተያያዥ ነገር አለ? ቀኑ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል፣ ለእምነት ተቋማትና ለፖለቲካ ፓርቲዎች ምቹ ነው? የሚለውን ጥያቄ ጉባኤው ከመወሰኑ በፊት መመልከት ይኖርበት ነበር። ጉባኤው ግን በተቃራኒው የተጓዘ ይመስላል። ይህ ቀን ማለትም 26/12/2005 ዓ.ም ግን ሰማያዊ ፓርቲ የአገር ሰላም እንዲሰፍን፣ ሰባአዊ መብት እንዲከበር፣ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን፣ ከአላግባብ የታሰሩ ዜጎች እንዲፈቱ፣ እኩልነት እንዲረጋገጥ፣ ሙስናና አገርን ወደ ኋላ ሊጎትቱ የሚችሉ ችግሮችን ለመቅረፍና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር ከመንግሥት እንኳ ሳይቀር ፍቃድ ጠይቆ ለ2ተኛ ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ የጠራበት ቀን ነበር። ጉባኤው ግን ይህን ሳያገናዝብ በመጥራቱ ለፓርቲው አባላት እስራት፣ እንግልትና ድብደባ ምክንያት ሁኗል። ፓርቲው የጠራው ሰላማዊ ሰልፍም በእስራትና በድብደባ እንዲቀየር አድርጎታል። ሙሉ በሙሉ ጥፋቱ የመንግሥት ቢሆንም የጉባኤው አባላት ለዚህ ተግባር ተባባሪ በመሆናቸው ተጥያቂ አድርጓቸዋል። ሌሎችን እናተ ጨምሩበት.......
በአጠቃላይ የጉባኤው ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አስፈላጊ ነበር የሚለውን ሁላችንም በራሳችን አስተያየት እንስጥበት እና እንማርበት። አስፈላጊ አልነበረም ለምንል ሰዎች ወደፊት እንዲህ አይነት ተያያዥ ክስተቶች እንዳይፈጠሩ ምን እናድርግ ለማለት ሃሳብ መለዋወጡ መልካም ስለሚሆን ለመነሻ ያክል የግሌን ሃሳብ አቅርቢያለሁ።

Thursday, August 8, 2013

የችግሮች መንስኤ እኛ እራሳችን ነን

ዛሬ ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግር እየጨመረ መምጣቱ ዓለምን ስጋትና ጭንቀት ውስጥ ከቷታል። ለአንዱ ችግር መፍትሔ ይሆናል ተብሎ የቀረበው ሃሳብ በሌላ በኩል ሊፈታ የማይችል ችግር ፈጣሪ ሲሆን መመልከት የተለመደ ነገር ነው። ምንም እንኳ /ከተለዩ ሰዎች በስተቀር/ ሰው በራሱ ችግር ለመፍጠር ተነሳሽ ባይሆንም ለመፍትሔም የዘገኘና ቆራጥነት የማይታይበት በመሆኑ ለችግሩ መበባስ መንስኤም ምክንያትም ነው። በዚህች አጭር ጽሁፍም የእኛ የችግር መንስኤነትን በአጭሩ ለማሳየት እሞክራለሁ። ሙህራን በዚህ ዙርያ ሰፊ ጥናት በማድረግ እንዲያቀርቡልን ግብዣየ በደስታ ነው።
  • እንደሚታወቀው እንደ አህጉራችን አፍሪካና አገራችን ኢትዮጵያ ሁላችንንም የሚያሳስበንና ጎልቶ የሚታየው የአስተዳደር/ፖለቲካዊ ችግር ነው። ሁሉም የፖለቲካ ድርጅት/ገዢው ፓርቲ/ ለነጻነት፣ ለሰላም፣ ለአንድነት፣ ለሰባዊ መብትና ለዲሞክራሲ እቆማለሁ ብሎ መነሳቱንና የህዝብ ድጋፍ ማግኘቱን ረስቶ የበፊቱንና የአለፈውን የአስተዳደር ዘመን በእጅጉ የሚያስመሰግን ሁኖ እናገኘዋለን። ዘረኝነትንና አድሎአዊነትን ለመዋጋት የተነሳ ድርጅት ከበፊቱ በበለጠ ችግር ፈጣሪ ሲሆን ጎልቶ ይታያል። ሙስናን ለመዋጋት የተነሳ ድርጅት ለሙስና መስፋፋት ዋነኛ ተዋናይ መሆኑ በእጅጉ ያሳስባል። ድህነትን ለማጥፋት የተነሳ ድርጅት ራሱን ከማበልጸግ ባለፈ የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ከቲዮሪ/theory/ ባለፈ መቀየር አልቻለም። ዲሞክራሲን አሰፍናለሁ ብሎ የተነሳ ድርጅት ሚድያ ላይ ከመናገር ባሻገር ህብረተሰቡን የዲሞክራሲ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ ግን አልቻለም። ምን አልባት ኢትዮጵያ በዲሞክራሲዊ አስተዳድር ስርዓት ትመራለች፣ ድህነት ቀንሷል ልንል እንችል ይሆናል፤ እውነት ነው የእኛም ትልቁ ችግራችን ይህ ነው። በመካከላችን 100% ልዩነት መኖሩ የተወሰነው የህብረተሰብ ክፍል በምቾት፣ በሰላም፣ በደስታ፣ በነጻነትና ዲሞክራሲ ሲኖር አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ደግሞ በእጅጉ በሚያሳዝን ሁኔታ በርሀብ፣ በችግር፣ በስቃይ፣ በአድሎአዊነትና በነጻነት እጦት ውስጥ መኖሩ ችግሩ ጎልቶ እንዲታይ አድርጎታል።
ለችግር መንስኤዎች እኛው ነን ያልኩበት ምክንያትም የፓርቲውን/የድርጅቱን ዓላም በሚገባ ሳንረዳና ሳንገነዘብ ከመጀመሪያው ጀምረን ይሁን ብለን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረጋችን ነው። ግማሾቻችን ደግሞ ሳይመቸን እንደ ተመቸን፣ ሳንጠግብ እንደ ጠገብን፣ ነጻነትና ዲሞክራሲ ሳይኖር በነጻነት እንደምንኖር ሁሉ እንደ ሄሮዶሳውያን ሺ ዓመት ንገስ፣ ከአለአንተ አገር ትገለበጣለች፣ ለህዝቡ ተቆርቋሪ የለም እያልን ችግሩን እንዲያስተካክል በግልጽ ከመናገር ይልቅ የማይገባውን የምስጋና ቅኔ ስለምናቀርብ፤ ከፊሎች ደግሞ በጊዜያዊ ጥቅም ተይዘው ችግሩን እንዳንመለከት ከለላ ስለሆነብንና መሰል ችግሮች ስላሉብን ለችግሩ መባባስ ዋነኛ ተጠያቂዎችም መንስኤዎችም እኛው እራሳችን ነን።
  • ለተለያዩ ችግሮች የመፍትሔ ሃሳብ ከምንጠብቅባቸው የእምነት ተቋማት ሳይቀር በመሪዎቻችን መካከል ዘርፈ ብዙ ችግሮችን እናገኛለን። ጥቂት የእምነት መሪዎች/አባቶች ነን ባዮች ከአለም ባለስልጣናት ባልተለየ መልኩ አስተዳደራዊ በደል በእምነት ተቋማቸው ላይ ሲያደርሱ መመልከት የተለመደ ነገር ሁኗል። ዘረኝነትንና ሙስናን ይዋጉልናል ያልናቸው ሰዎች ለችግሩ መፋጠን ዋነኛ አካል ሁነዋል። ቤተ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር በተሰጠችው መመርያ ተጠቅማ ለአለም ሰላም የማደል ፀጋ ቢኖራትም ዳሩ ግን እነዚያ ጥቅመኞች ፀጋዋን ለዓለም እንዳታድል አዚም ሁነውባታል።
ለዚህም ችግር መንስኤ እኛው የእምነቱ ተከታዮች ነን። ለምን ቢባል በተለያየ ዘርፍ ላይ ለሚገኙ የእምነት ተቋም አስተዳዳሪዎች ፊት በሙስና፣ በስርቆትና በብልሹ አስተዳደር ስለበለጸጉ ሰዎች እናወራለን፣ እንተርክላቸዋለን። በእነዚህ ነውረኛ ሰዎች ላይም ምንም አይነት የእምነት ሃላፊነታችንንና ግዴታችንን መወጣት ባለመቻላችን ሌሎች እንደማበረታቻ ቆጥረውታል። በእነዚህ እና መሰል ምክንያቶች ችግሮች እንዲበባሱ የእኛ አስተዋጾ ቀላል እንዳልሆነ መገንዘብ ይቻላል።
  • ወደ ባዕድ ሀገር በስደት የሚጎርፈው ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ሀገር ቤት ሰው የማይኖር እስኪመስል ድረስ ፍላጎቱና ፍልሰቱ ከፍተኛ ሁኗል። ለዚህ ችግር በዋናነት የመንግሥት አስተዳደራዊ ድክመት ቢሆንም እኛም የበኩላችንን ድርሻ ባለመወጣታችን የመጣ ትልቅ ችግር ነው። በስደት የሚኖሩ ወገኖች የስደትን አስከፊነት እያወቁ ነገር ግን በሀገር ቤት ለሚኖሩ ወገኖቻቸው ችግሩን በሚገባ አለማስረዳት፣ ወደ ሀገር ቤት በሚሄዱበት ጊዜም የተለየ ለብሰውና መስለው መታየታቸው እና የሚሰሩትን የሥራ አይነት እንኳ በትክክል አድካሚነቱንና አሰልችነቱን አለመናገር ለሌሎች ከሀገር መውጣት ምክንያት ሁኗቸዋል። ስለዚህ የሆነውንና የሚሆነውን በትክክል መረጃ መስጠት ብንችል ወገኖቻችን በይሆናልና በማይሆን ተስፋ ከሀገር ወጥተው የስደትን አስከፊ ህይወት ተጠቂ ባልሆኑ ነበር። ስደት ምንልባት በኢኮኖሚ የተሻለ ነገር ሊኖረን ይችል ይሆናል እንጂ የሰላም ኑሮ ግን መኖር የሚቻለው ተወልደው በአደጉበት ሀገር ነው። በስደት ህይወት የባህል፣ የእምነት፣ የአለማዊነትና የቋንቋ ተፅዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ የተረጋጋና ሰላማዊ ህይወት መምራት በጣም አስቸጋሪና ከባድ ነው። በዚህም የተነሳ በጭንቀትና በውጥረት የሚኖሩ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም። ስለዚህ ሰውን ወደ ስደት ህይወት መጋበዝ በጭንቀትና በሃሳብ እንዲኖር መፍረድ   የሚል  ድምዳሜ  ቢሰጥ  ያንሳል  እንጂ ማጋነን አይሆንም።
በአጠቃላይ እኛ ሁላችንም ብንችል የችግር መፍትሔዎች እንድንሆን ባንችል ደግሞ የችግር መንስኤዎች እንዳንሆን የራሳችንን በጎ አስትዋጾ ማድረግ ይኖርብናል። ለችግር መፍትሔ ይሆናሉ ያልካቸውን 2 ላንሳና ሌላውን እናንተ ቀጥሉበት።
  1. ችግሩን በትክክል መረዳት፦ ችግሩን ከስር መሰረቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ በአጠቃላይ ሀገራዊ ጉዳቱን መረዳትና ችግሩ እንዳይበባስ የራሳችንን አስተዋጾ ለማድረግ ችግሩን በትክክል መረዳት ይጠበቅብናል። ሙህራን “ችግሩን ማዎቅ የመፍትሔ 50% ነው” እንዲሉ ችግሩን በትክክልና በጥልቀት መረዳት ካልቻልን መፍትሔ በቀላሉ ለማግኘት አስቸጋሪ ስለሚሆን የችግሩን የት፣ መቼ፣ እንዴትና ወዴት የሚሉትን ጥያቄዎች በማንሳት ችግሩን ከመሰረቱ ማዎቅ ከሁላችን የሚጠበቅ ተግባር ነው።
  2. ችግሩን ለማሶገድ በቆራጥነት መነሳት፦ ችግሩን በትክክል ከተረዳን መፍትሔ ለማምጣት ደግሞ በቆራጠነት መነሳት ይኖርብናል። ፍራትን፣ ቸልተኝነትን፣ አይሆንም ባይነትን፣ አድርባይነትን፣ ጥቅመኝነትንና ዘረኝነትን ከውስጣችን አሶጥተን ለሀገርና ለተተኪ ትውልድ በሁሉም በኩል የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ቆራጥነትና ሰማትዕነት ያስፈልጋል። የማንም ርዳታ ሳያሻን በራሳችን ተነሳሽነት ሀገራዊ ሃላፊነታችንን ለመወጣት እና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ሁላችንም ቆርጠን መነሳት ይኖርብናል።.........................+++

Thursday, July 4, 2013

FACTS ABOUT MORSIS YEARS IN POWER AND WHAT OBAMA SAID

Mohammed Morsi (Photo: Egyptian State Television / AP Photo)

  1. 30th June 2012: Mohamed Morsi wins the presidential elections in Egypt with 51.7 percent of the vote. The next day he is sworn in as the country's first civilian and first Islamist president.
  2. 12th August: Morsi revoke a decree that gave military council the real power in the country, removing council leader Hussein Tantawi, who has run the country since President Hosni Mubarak had to go in February 2011.
  3. 22, November: Morsi issues a decree giving him greater powers.
  4. 30th November: An Islamist-dominated Constituent Assembly adopts a new constitution.
  5. 8 Dec: Morsi repeals the controversial fullmaktsdekretet.
  6. 15th and 22 December: In a referendum approves 64 percent of voters the new constitution. The opposition refuses to accept the result. Several killed in clashes between opponents and supporters of Morsi.
  7. 24th January 2013: Violent clashes between protesters and police in conjunction with the second anniversary of the outbreak of the revolution.Almost 60 people are killed in the course of a week.
  8. 5 April: Four Christians and Muslims killed in religious clashes.
  9. 2 June: Egypt's constitutional court invalidates the election of the Senate, the only part of the National Assembly still sitting together, and the Constitutional Assembly.
  10. 21st June: Tens of thousands of Islamists demonstrating in support of Morsi.
  11. 30th June: Tens of thousands demonstrate against the president on the first anniversary of his election victory. According to the Minister of Health, 16 killed.
  12. 1 July: The Opposition gives Morsi a day to resign. The military gives the president two days to resolve the situation.
  13. 3 July: Morsi is deposited in a military coup and put under arrest. (Source: AFP Manager) (NRK-NTB)   
Obama calls not overthrow a coup
Barack Obama was careful not to make direct distance from the deposition of Morsi.Photo: Evan Vucci / AP
United States urges all Americans to leave Egypt for fear of unrest after President Morsi ouster Wednesday night.
President Barack Obama avoided calling the overthrow of President Mohamed Morsi for a coup, when he last night called on the Egyptian military to give power back to a democratic civilian government as soon as possible.
Obama was careful in the use of language when he comments deposition night and said he was "deeply concerned" over the military had removed the government and the constitution set aside.
"I ask the Egyptian military to act quickly and responsibly to give the power back to a democratically elected civilian government as quickly as possible through an inclusive and transparent process and to avoid arbitrary arrests of President Morsi and his supporters", Obama said.
The U.S. president said he has ordered a review of what the Egyptian military actions will have and impact on U.S. military aid to Egypt.
United States contributes around $ 1.5 billion in annual economic aid to the Egyptian military.
In U.S. law, the U.S. can not provide financial assistance to any country whose leader is deposited in a coup.
The article continues below.


President Barack Obama met with his counselors in an emergency meeting in the White House to discuss the developments in Egypt.Photo: Pete Souza / White House / Handout / Reuters
Bs Americans leave the country
The U.S. State Department sent a night out a warning to U.S. citizens to leave the country.
It is not clear how many Americans living in Egypt, but it's probably about several thousand, writes New York Times .
The warning against travel to Egypt at all regarded as a serious blow to Egypt's already hard-hit tourism industry.

Evacuate Embassy
The United States has also started to evacuate the so-called "non-essential" employees at the embassy in Cairo, as well as family members of the embassy staff.
U.S. embassy in Cairo has been closed for several days after demonstrations against President Morsi began last week.
Last Friday was an American student, 21 year old Andrew pochta, killed with a knife during a demonstration in Egypt's second city, Alexandria. 

Wednesday, July 3, 2013

Ethiopia after Meles

By Obang Metho
I would like to thank the Chairman of the Committee on Foreign Affairs, Congressman Edward Royce, and all ranking members of the Subcommittee on Africa, Global Health, Global Human Rights and International Organizations for this important opportunity to examine the Ethiopian Government’s observance of democratic and human rights principles in post-Meles Ethiopia.

I want to especially thank Congressman Christopher Smith, the Chairman of the Subcommittee on Africa for his extraordinary leadership in bringing the case of Ethiopia to the attention of this subcommittee once again; particularly in light of the many pressing global issues. In 2006, Congressman Smith worked hard to bring this issue all the way from subcommittee to the House, where it faced obstacles and died. I hope this time, something more concrete and productive can be accomplished for the betterment of both our countries.

                                             Obang Metho, pic by Awaramba Times 

In 2006, I gave testimony at that previous hearing in regards to the massacre of 424 members of my own ethnic group, the Anuak, in 2003, perpetrated by members of the Ethiopian National Defense Forces. I also testified regarding the ongoing crimes against humanity and destruction of property and infrastructure in the Gambella region of Ethiopia; however, because similar abuses were being perpetrated in other places in the country, I also spoke of the 193 peaceful protestors who were shot and killed as they peacefully protested the results of the flawed 2005 national election and the repression in Oromia. This also included testimony regarding the imprisonment of opposition leaders, including Dr. Berhana Nega, who is sitting next to me today.  

Now I am here once again to testify about these same kinds of issues because Ethiopians have only seen increasing restrictions to their freedom and a continuation of government-sponsored human rights violations in every region of the country. This includes the illegal eviction of great numbers of Ethiopians from their ancestral homes and land, causing great hardship to the people. It also includes egregious human rights atrocities in places like the Ogaden [Somali] region, which is blocked from the outside world by the regime. It has obstructed the media from reporting on the great suffering of the people being perpetrated by government forces, which has been described as a silent genocide. Two Swedish journalists were arrested, detained and charged as terrorists before being released last year.  However, the Ogaden is not alone for every region of the country has become a victim to this regime.

Sadly, little, in terms of rights, has changed post-Meles. The only change is that he is no longer here.  Although the rapid decline in freedom and rights was led by Meles, he and his cabinet and ministers established an apparatus of strong-armed control that continues to reach from the top offices of the federal government to rural villages throughout Ethiopia. That infrastructure of repression, which carries out much of the day-to-day enforcement of EPRDF control and the perpetration of human rights violations, is still in place and marks the near achievement of a secretive and chilling plan put into motion in June 1993 under the name: TPLF/EPRDF’s Strategies for Establishing its Hegemony & Perpetuating its Rule[i],which was said to have been given to all their cadres for its execution. An abridged translation of the 68-page Amharic document is now available online.

This plan, based on Marxist ideology, was brought to our attention by one of the members of the TPLF who reported to us strict adherence to this plan by its cadres. The plan aligns closely with the nature of the TPLF when they were still fighting in the bush as well as the Ethiopia of today.
Prior to defeating the brutal Derg regime in 1991, Meles led the Marxist-Leninist based rebel group, the Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF), also so known for its brutality in the bush that the U.S. State Department had classified them as a terrorist group at the time. When they took over power, they formed a new coalition party made up of separate ethnic-based parties. It was called the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and was meant to appear to be a multi-ethnic government but in fact, it has been controlled from the beginning by the TPLF who have never abandoned the goal of perpetual hegemony.

The EPRDF’s structure was based around ethnically defined regions and political parties, but at the grassroots level, all regions and parties, though appearing to be led by leaders of the same ethnicity as the region, were instead pro-TPLF/ERPDF puppets, who implemented their policies. By its nature, this division of Ethiopia by ethnicity was a guise meant to dupe the public and the west by its appearance of being democratic; however, in practice, it has contributed to the prolongation of ethnic-based divisions while strengthening the power of the TPLF, assuring its control of the EPRDF even though Tigrayans are a minority, making up only 6% of the total population. However, this does not mean the TPLF speaks for many Tigrayans who have become disillusioned with the TPLF/EPRDF. 

In short, the TPLF’s plan of revolutionary democracy, which is more closely aligned with the Chinese model than the liberalism of the west, was clearly designed to achieve perpetual hegemony over every aspect of Ethiopian life. In the above-stated plan, they warn that they can achieve their goals “only by winning the elections successively and holding power without let up.” They warn, “If we lose in the elections even once, we will encounter a great danger... [so] we should win in the initial elections and then create a conducive situation that will ensure the establishment of this hegemony.” In 2010, the TPLF/ERPDF successfully accomplished this goal and won their fourth election with an alleged 99.6% of the votes and all but one of the 547 seats in the Ethiopian Parliament.  

This also was accomplished through gaining control every sector of society: the media, all aspects of government and civil service, all political space, elections, the judiciary, the passing and interpretation of laws to suit their goals, the financial sector, education, the military, the economic sector, religious groups, civic society, government ownership of all land and government control in the extraction of natural resources. The principles upon which America was founded are absent in Ethiopia despite all the democratic rhetoric.

The TPLF/EPRDF is more in control today than it was in 2006 and continues to hold that power despite the death of their central figure. It has become near to impossible to find any political space for the development of a viable alternative to the TPLF/EPRDF because dissenters, activists or anyone speaking for change will be put in jail. It has become a full-blown autocracy. Anyone who attempts to speak up is silenced. All has been justified by saying that Ethiopia has double digit economic growth and that they have met their millennium goals and that the people are too ignorant to understand how they will eventually benefit; however, the people know that this is not balanced growth but instead has “filled the pockets and bellies” of government supporters as laid out in the 1993 plan. Claims of economic gains also serve to minimize or cover up the reality on the ground of the increased poverty of the majority.  Supporters of the TPLF/EPRDF policies and tactics are rewarded while non-supporters are penalized in a variety of ways. The most marginalized masses are ignored unless they become an impediment to the TPLF/ERPDF plan of exploitation of land or natural resources. Here is an explanation of that strategy from the original TPLF/ERPDF plan:

The combined strength of the State and Revolutionary Democracy’s economic institutions should be used either to attract the support or to neutralize the opposition of the intelligentsia.  We should demonstrate to it that our economic strength could serve its interests, and, in the event of its opposition to us, its belly and pocket could be made empty.

Examples of the practice of the above strategy are rampant. According to a Human Rights Watch[ii] report, following the 2010 election, even humanitarian aid was linked to party membership.

Record numbers of refugees are leaving the country, regardless of the risks, because so little opportunity exists for the average person, let alone for more outspoken dissenters. Laws such as the Charities and Societies Proclamation[iii] have literally closed down civil society, replacing institutions with TPLF/ERPDF controlled look-alike organizations. A vague anti-terrorism law[iv] has been used to silence journalists, editors, democracy activists, religious leaders and opposition members by intimidating them, arresting them or charging and imprisoning them as terrorists. Examples are our heroes of freedom such as Eskinder Nega, Reeyot Alemu and Andualem Arage.

Into this highly controlled milieu, the new Prime Minister, Hailemariam Desalegn, has emerged. He is neither Tigrayan nor is he part of the old guard of TPLF loyalists but instead comes from the South, helping to counter accusations of TPLF domination of the EPRDF. Reportedly, his appointment was hotly contested; however, because he had held the position of Deputy Prime Minister it may have provided the least controversial transition. Insider information reports he has little power and that his actions are all closely monitored by the TPLF central committee. As another means of control, three deputy prime ministers of different ethnicity were appointed and are said to hold more power than the prime minister.  Reports have also surfaced that power struggles within the party leadership have split the top power holders and remain unresolved. These intraparty conflicts could deepen as the next election comes closer, with unpredictable, but possibly dangerous results. Hoping that this problem will resolve on its own is unrealistic and a recipe for disaster. 

The TPLF/ERPDF has so effectively constructed a system of repression in Ethiopia that it will likely carry on for awhile; however Meles, the driving force who charmed the west while terrorizing the people, remains their main visionary leader. Billboards around Addis Ababa show his picture and the TPLF/ERPDF continues to elevate his legacy, possibly because no one else within the party has been able to articulate another, more timely or urgently-needed vision.This opens them up to new challenges from the dissatisfied majority that they may not be able to dodge. Intraparty conflicts may also further exacerbate the situation. Add to that pressure from the outside, like from Egypt, neighboring countries or others and the situation may either explode or implode without reforms. Although the TPLF/EPRDF has shown little openness to reforms, with enough pressure from the people and donors like the U.S., it might create a win-win situation to bring about such reforms without violence, chaos and a spillover effect in the Horn of Africa.

The road to democracy and respect for human rights in Ethiopia must be solved by Ethiopians, but the U.S. has a role to play as well. I believe the current U.S. policy of quiet diplomacy will actually contribute to a worse outcome. We should learn from what happened in the Arab Spring, when forces of a frustrated public joined together to oust Egyptian President Hosni Mubarak. It took many by surprise, especially those who had sided with an authoritarian regime rather than the people, thinking Mubarak was so powerful that he could not be brought down. This alliance with an authoritarian regime makes it much more difficult in the aftermath to reestablish a meaningful partnership with Egyptians that goes beyond giving large amounts of foreign aid.

Undoubtedly, many Ethiopians attribute U.S. support to Ethiopia, including partnership in the War on Terror, as a means that has prolonged the life of a repressive, undemocratic regime. Will the U.S. be pro-active in aligning with the people; something that will help sustain a long-term relationship with Ethiopians? Unfortunately, the tendency of most entrenched groups and their supporters, foreign or native, is to continue the status quo without any change; however, in Ethiopia, there is a window of opportunity before the next election in 2015 to set the stage for meaningful reforms. The U.S. and other donor countries should not simply stand by, using the rationale that there is no viable alternative to work with because the TPLF/ERPDF has been so effective in blocking access to political space and will not easily give up on this.  This must be taken into consideration for how can you build an alternative in this kind of repressive environment? You cannot put someone out in the middle of nowhere with no material and tell them to build something. It will not work.

With these limitations in mind, the Ethiopian public, both at home and in the Diaspora, are now working to bring the change. Some of that change can be seen from what happened last week in Addis Ababa when Ethiopians came out in mass numbers to peacefully rally for freedom and justice in Ethiopia based on a call from the newly emerging Blue party. With minimal resources, the Blue party reached out to the public in an inclusive way and the groundswell of response from ethnically, politically and religiously diverse Ethiopians surprised even them.They called on the people and the people answered. Yet, the TPLF/ERPDF warned that Muslims who joined together with Christians and others in the rally were extremists.  This defies the reality on the ground.

For the last year, Ethiopian Muslims have been peacefully rallying in their compound, asking for freedom to practice religion without government interference into their internal affairs. In violation of the Ethiopian Constitution, the TPLF/ERPDF has been choosing their religious leaders, ensuring those leaders were pro-government. The TPLF/ERPDF has done the same within the Ethiopian Orthodox Church leading to the church breaking into two divisions—the government approved church in Ethiopia and the other in exile here in the U.S. – a divide and conquer strategy of gaining hegemony of religious groups addressed in the TPLF/EPRDF master plan of 1993. Within that plan, religious groups were to be “used to disseminate the views of Revolutionary Democracy...and if that is not possible we should try to curtail their obstructionist activities…Without denying them due respect, we should mold their views, curtail their propaganda against Revolutionary Democracy, and even use them to serve our end.”

The TPLF/ERPDF government will do anything to label the Muslims as extremists and radicals to be feared by the west; however, Ethiopian Muslims, Christians and Jews have lived together for thousands of years in harmony. We do not only share the land but we share blood. We are a family. We are brothers and sisters.

In twelve months of rallying, these peaceful Muslim protestors have never destroyed anything or hurt another person. They are not making a stand for Sharia law but instead for a secular state where all people will be free and where there is no government interference in the practice of any religion. Yet, the TPLF/EPRDF fears unity between diverse religious groups. 

Reports have emerged of the TPLF/ERPDF’s intentions to divide people of different religious faith and to alarm the west by staging events themselves while blaming others. For example, inside reports allege that when Ethiopian Muslims were going to rally in front of the U.S. Embassy, they found out that pro-government forces were going to burn the American flag so they called off the entire rally. An eyewitness to the killing of Christians in 2007, reported to be by Muslims in the Oromo region of the country, were recognized by a relative to not be Muslims at all but government supporters.

I personally spoke to that survivor. It preceded the invasion into Somalia and is seen as an attempt to dupe the west. It must be understood that it profits this regime to do violence in the name of their opponents. Here is another example reported in Wikileaks where the U.S. had knowledge that the TPLF/ERPDF government had set the bombs in Addis Ababa several years ago so as scapegoat government opponents. They used it to justify the arrest of Oromo leaders as terrorists and to show a rising incidence of terrorist acts in Ethiopia, even though it was phony. Duping the west into supporting the TPLF/ERPDF was part of their original strategy laid out in the 1993 plan and is part of the reason for becoming a pseudo-democracy.

Division between ethnicities, regions, political parties and religious groups is the lifeblood of the TPLF/ERPDF. For the government to gain power and control, they are trying to alienate the people from each other and spread rumors regarding the makeup of those who are protesting. Just as they are calling Muslims extremists and terrorists, they are now trying to label the Blue party, to separate them from others, by accusing them of being funded by foreigners like Egypt. The fact that Christians and Muslims are rallying together for freedom and justice for all Ethiopians is a real threat to their existence. These kinds of tactics by the government are a sign that the status quo cannot continue and will be challenged in increasing unity among Ethiopians. The donor countries, including the US, should align with the people.This means supporting the people who are working from within and those who are trying to resolve the problem peacefully, without violence. 

The proper sequence of reforms is critical to the success of the outcome. 
1. Intellectual reform must come first, which means the people must have access to information and have the freedom to express it—the first freedom to be attacked by dictatorships and the first that needs to be restored to bring about change.

2. The second must be political reform; opening up political space so the choice of the people is reinstated. Then they are free to choose political leaders and groups who represent their interests and the interests of the country. 

3. The third is constitutional reform which must rewrite, redefine or reinstate the most inclusive and beneficial relationship between the people and the state in the form of this “constitutional contract”; a contract which upholds the rights of the people and protects the people from the state, similar to African models where it is assumed anyone can become tyrannical so checks and balances must be established to control the power of the government, ensuring participatory democracy. 

4. The fourth is institutional reform; meaning reforms of the judiciary, the parliament, the military, civil services, and other institutions where regime cronies are now in control.  Institutions must be independent of the state or party for change to be accomplished and made sustainable. 

5. Lastly, economic reforms are necessary but will not be inclusive until the other reforms are implemented, making the system more transparent, accountable, and just; unlike in places like Russia, Ivory Coast, Indonesia, Yugoslavia, Cameroon, Rwanda and the Philippines where economic advances were made; yet, regime cronies still controlled the institutions, the political system and the justice system, staging the conditions for a reversal of power and the re-emergence of repression and cronyism.
Poverty and corruption in Ethiopia will also increase the pressure for explosion. Recently, Kofi Annan spoke about the cost of corruption to the African people.  Ethiopia is a primary example.  Although many quote statistics of economic growth in Ethiopia, most of it is in the hands of a few.  Prior to the release of the report by the Global Financial Task Force in their report titled: Illicit Financial Outflows from Developing Countries Over the Decade Ending in 2009, they stated on December 5, 2011 the following in regards to Ethiopia:

“The people of Ethiopia are being bled dry. No matter how hard they try to fight their way out of absolute destitution and poverty, they will be swimming upstream against the current of illicit capital leakage.”[v]

Their report reveals that Ethiopia lost US11.7 billion in illegal capital flight from 2000-2009 and illicit financial outflows from Ethiopia nearly doubled in 2009 to US$3.26 billion—double the amount in the two preceding years—with the vast majority of that increase coming from corruption, kickbacks and bribery. When it comes to transparency, it does not exist in Ethiopia.   
Here is another example.  Human Rights Watch found evidence that World Bank money, which was to be used for services, was instead used by the government to displace the people from their land, later given to foreign and crony investors. Five villages in the Gambella region, hard hit with land grabs, accompanied by human rights violations, made an appeal to the World Bank regarding the improper use of its funds. An independent inspection panel investigated the grounds for the appeal for the World Bank.  After meeting with the local people who had been displaced to refugee camps in Kenya and South Sudan, they recommended a full investigation after finding substantial evidence of the misuse of World Bank funds. Now the Ethiopian government has refused to cooperate. All donors to the World Bank should look into this because this is your money. If they have nothing to hide, why would they not allow an investigation?
People on the ground in Ethiopia live in fear of this regime, but many are coming to the point that they can no longer endure life without change and are willing to take a stand.  Prior to the Blue party’s recent rally, a 26-year-old recent graduate sent me his thoughts.  He said:

Obang, it is now just four hours before we go out to rally.  We don’t know what will happen but this may be my last message because the last time I went out I went with three of my friends and I was the only one who came back.  That was seven years ago after the 2005 election. I may be the one not come back this time but I am not afraid. I am looking at it like going into a war zone, but the only difference is the other side has a gun and we have nothing.  If they shoot, I have nothing to deliver. This is the kind of country we live in.  But, we have the moral high ground and this is what is making me go out. I want someone to know.

Ethiopia is a country which relies on the US as its number one supporter and here is one of their brave, but peace-loving heroes, going out not knowing what will happen to him and those with him. Most of you have met Ethiopians here in Washington D.C. as thousands of Ethiopians live and work in this city. They pay taxes to the same government that for too long has overlooked the serial violations of human rights and the emergence of a full-blown dictatorship

Ethiopians have struggled under dictatorship for 40 years. With the death of Meles and the appointment of Prime Minister Hailemariam Desalegn until the next election in 2015, Ethiopians may have been given the most opportune moment in 21 years for change; however, if Ethiopians—or donor countries genuinely wanting to see democratic reforms—step back, waiting to see what will happen under this new arrangement of power, rather than actively creating a process of change that is owned and managed by the people of Ethiopia, this opportunity will most likely be hijacked and the “system” of repression will continue with the same or new “strongmen” at the helm.  The only acceptable outcome for the Ethiopian people is nothing short of the transformation of Ethiopia to a new society and a New Ethiopia wherehumanity comes before ethnicity or any other distinctions for no one is free until all are free!

This is a time when the U.S. should use their influence to put pressure on the Ethiopian government for reforms rather than waiting for simmering tensions to explode.  Support for a people-driven process is the best alternative to bring lasting change to Ethiopia, more sustainable peace to the Horn and a better ongoing partnership with the US.

Thank you!
Please click the link or open the attachment to read the entire statement: :http://www.solidaritymovement.org/downloads/130620-Testimony-before-Subcommittee-on-Africa.pdf 









I am appealing to each of you to forward it to all your friends. If you do, you will not just be giving a voice to our beautiful people, but you would be doing justice to our humanity. Knowing the truth is overcoming the first obstacle to freedom! 
Thanks so much for your never-ending support. Don’t give up. Keep your focus on the bigger picture and reach out to others and listen! Care about those who are suffering. Think about our family of Ethiopians and humanity throughout the world—they are YOU! There is no “us” or “them.” This is at the heart of the SMNE.

Sincerely your,
Obang
Executive Director of SMNE
E-mail: obang@solidaritymovement.org
http://www.solidaritymovement.org

Monday, June 3, 2013

የሰማያዊ ህዝባዊ ሰልፍ ጠቀሜታ




ትናት ግንቦት 25፣2005 ዓም የሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የፓርቲው ደጋፊዎችና የገዝውን ፓርቲ አገዛዝ በመቃወም በዋናነት የተለያየ ምክንያት ተፈልጎላቸው በእስር ቤት የሚገኙ የፖለቲካም ሆኑ ሌሎች እስረኞች እንዲፈቱ፣ ዲሞክራሲ በአገራችን ይስፈን፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይግባ እና ሌሎችንም ችግሮች በማንሳት ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል። ይህንንም የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እና ድረ ገጾች በስፋት ዘግበውታል።

1, ETV
ኢቲቪ ዜናውን በመዘገቡ ሊመሰገን ይገባል። በዜናው ላይ ያስተላለፉት መልክት የራሱ የሆነ ሌላ ጥያቄ ቢያስነሳም።

2, የኢሳት/ESAT ዘገባ

3, የጀርመን ሬዲዮ ድምጽ እና ሌሎችም ድርህረ ገጾች በስፋት ገልጸውታል።

በአጭሩ የዚህ ህዝባዊ ሰልፍ ጠቀሜታው

1, ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ፣ ለነጻነቱና ለዲሞክራሲ መስፈን ፍራቻን አስወግዶ በአንድነት መጓዝ እንዳለበት አመላካች በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው።

2, ለገዥው ፓርቲ፦
  • በአዓለም መንግስታት እይታ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
  •  ህዝቡ ምን ያክል እንደተማረረና ጥላቻ እንዳለው እንዲረዳ ያደርገዋል።
  • ህብረተሰቡን የሚጠቅም ስልታዊ እቅድ እንዲነድፍ/ እንዲከተል አቅጣጫ ጠቋሚ በመሆኑ ሰልፉ ለሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ጠቀሜታው የላቀ ነው።






Friday, May 31, 2013

ስለአባይ ምን ተባለ?

                                                                                           በከበደ ካሳ
https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEj9wbVH3TqueRjGM3LyUpt3jQf2OavsAU0D0Unns3zubiU2JSQAzNnDMH0mM4myVrtf8LneYC6FurAXKUKjLG4p75zsxhM65wMVlYJG8O811fYb03HLA5tmNM3QcQQJE6Y1VbZwOJgJBNY/s1600/%E1%8A%95%E1%8C%8C.jpg
ኢትዮጵያ ግንቦት 20/2005 የአባይ ወንዝን የተፈጥሮ አቅጣጫ መቀየሯ የአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንና ጉዳዩ የሚመለከታቸዉ ሀገራት መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል፡፡ ዋናው ጉዳይ ምሽት ላይ አልጀዚራ በኢንሳይድ ስቶሪ /inside story/ ፕሮግራሙ ከኢትዮጵያ አቶ በረከት ስምዖንን፤ ከግብፅ ላማ ኤል ሃሎንና ከእንግሊዝ ሊዮ ፓስካልን በማስገባት ዉይይት ያደረገበት ነው፡፡ በዚህ ላይ በኋላ እመለስበታለሁ፡፡ አሁን ግን መገናኛ ብዙሃን፤ ግብፅና ሱዳን ምን አሉ የሚለዉን እንመልከት፡፡

በጉዳዩ ላይ ሰፊ ዘገባ የሰጠው አህራም የተባለዉ የግብፅ ድረ-ገፅ ነው፡፡ ቢቢሲ፤ አልጀዚራና ዋሽንግተን ፖስትም እንዲሁ፡፡ ሁሉም ታዋቂ መገናኛ ብዙሃን በተለያየ መጠን ለጉዳዩ ሽፋን ሰጥተውታል ማለት ይቻላል፡፡ ከብዛታቸውና ከምንጫቸው ተመሳሳይነት አንፃር የያንዳንዱን ዘገባ አቅጣጫ ከማየት ይልቅ በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት አስተያየታቸውን ወደሰጡት ግለሰቦች አትኩሬአለሁ፡፡
ከላይ ከቁንጮው እንነሳ፡፡ ማለቴ ከግብፅ መንግስት አቋም፡፡ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ያወጣው መግለጫ አሁን በአባይ ወንዝ ላይ እየተካሄደ ያለው ግንባታ በውሃ መጠኑ ላይ መቀነስን ሊያስከትል የሚችል እንዳልሆነ የሚገልፅ ነው፡፡ በአባይ ላይ የሚገነባ ማንኛውም ፕሮጀክት ከመጀመሩ በፊት የወንዙን አቅጣጫ በማስቀየር ቦታውን ለግንባታ ምቹ ማድረግን ይጠይቃል ብሏል መግለጫው፡፡ ስለሆነም ከተለመደው ውጭ የሆነ አዲስ ነገር የለም የሚል ይመስላል፡፡
የግብፅ ካቢኔም በጉዳዩ ላይ ትናንት በዝግ ከመከረ በኋላ ባወጣት ቁራጭ መግለጫ የግድቡ ግንባታ ተጀመረ ማለት ግብፅ እውቅና ሰጥታዋለች ማለት አይደለም ብሏል፡፡ ያም ሆኖ የግብፅና ሱዳን የውሃ ድርሻን የማይቀንስ እስከሆነ ድረስ ማንኛዉንም የልማት ፕሮጀክት እደግፋለሁ ብሏል ካቢኔው፡፡ ካቢኔው ጨምሮ እንደገለፀው ለማንኛውም የሶስትዮሽ ኮሚቴውን የጥናት ሪፖርት ይፋ መሆን እንደሚጠብቅ ገልጧል፡፡ ሪፖርቱን ተከትሎ የሚይዛቸዉን አቋሞች /የሚወስዳቸዉን እርምጃዎች/ ከወዲሁ እንዳዘጋጀም ካቢኔው ጠቁሟል፡፡ ምን እንደሆኑ ፍንጭ ከመስጠት ቢቆጠብም፡፡ በዝች መግለጫ መጨረሻ የገባችዉ አረፍተ ነገር ደግሞ “ግብፅና ሱዳን በአንድ ልብ ሆነን በጉዳዩ ላይ ተባብረን እየሰራን ነዉ” ትላለች፡፡ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ እያደላች ነው የሚለዉን ዘገባ ለማጣጣል የገባች አረፍተ ነገር ሳትሆን አትቀርም፡፡
አሁን ዘግይቶ እንደተረዳሁት ደግሞ ዛሬ ግንቦት 22/2005 ፕሬዝዳንት ሙርሲ ከተመረጡ ሚንስትሮች ጋር በዚሁ ጉዳይ ላይ ለመምከር ቀጠሮ ይዘዋል፡፡
የሃገሪቱ የሹራ ምክር ቤት ደግሞ በመጭው እሁድ በዚሁ ጉዳይ ላይ ለመምከር የአስቸኳይ ስብሰባ ቀን ቆርጧል፡፡ በስብሰባው የውጭ ጉዳይና የደህንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎችን ጨምሮ 6 ኮሚቴዎች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል፡፡
እኔ እንዳገኘሁት መረጃ ከሆነ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሃገሪቱ ያሉትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ሞሃሙድ ድሪርን አስጠርቶ በጉዳዩ ላይ ቃላቸዉን ተቀብሏቸዋል፡፡ ምስኪን! ምን ብለዉ ይሆን? የሚኒስቴሩ የስራ ሃላፊዎች ከበው በጥያቄ ሲያዋክቧቸው፡፡ እንደ መረጃው ሰዎቹ በኢትዮጵያ ዉሳኔ መከፋታቸዉን ለአምባሳደሩ ገልፀውላቸዋል፡፡
ከአባይ ወንዝ የፍሰት አቅጣጫ ማስቀየር ጋር በተያያዘ ስማቸው በተደጋጋሚ የተነሳዉ የግብፅ ውሃና መስኖ ልማት ሚንስትሩ ሞሃመድ ባሃ ኢልዲን ናቸው፡፡ እሳቸዉ የንግግራቸው መጀመሪያ ያደረጉት ግብፅ በጥቅሟ ላይ የሚመጣን ማንኛውንም አይነት ፕሮጀክት እንደማትደግፍ መግለፅ ነው፡፡ ይህ አቋማቸው እንዳለ ሆኖ የወንዙ የፍሰት አቅጣጫ መቀየሩ ግን ለግብፅ ምንም ጉዳት እንደሌለው ለጋዜጠኞች አረጋግጠዋል፡፡ “የተለመደ የግንባታ ሂደት መገለጫ ብቻ ነዉ” ብለውታል፡፡

የአንድ ሃገር ሚኒስትር ከዚህ በላይ ሊሉት የሚችሉት በጎ ነገር ሊኖር አይችልም፡፡ የሃራቸውን ጥቅም የሚጎዳ ነገር ካለ እሱን መቃወም አለባቸው፤ ከሚጠቅማቸው ጋር ደግሞ መተባበር፡፡ እሳቸው ያሉትም ይህንኑ ነው፡፡ አሁን በግብፅ ላይ የተደቀነ አደጋ የለም፤ የጋራ ኮሚቴው ሪፖርት እስከሚወጣ እንጠብቃለን ነው ያሉት፡፡
እኝህ ሰው በቅርቡ በሃገሪቱ በተደረገው የስልጣን ሽግሽግ ባሉበት እንዲቆዩ ሲደረጉ እንኳን ደስ አለዎት በማለቴ የተረቡኝ እንደነበሩ አስታውሳለሁ፡፡ ሰውየው ምንም ያህል ትችት ቢሰነዘርባቸውም ስለኢትዮጵያ ያላቸውን በጎ እይታ በአደባባይ ከመግለፅ ያልተቆጠቡ ናቸው፡፡
ሌላዉ በዚህ ጉዳይ በንቃት የተሳተፉት በኢትዮጵያ የግብፅ አምባሳደር ሞሃመድ እድሪስ ናቸው፡፡ የህዳሴው ግድብ ግብፅ የግዷንም ቢሆን ልትቀበለው የሚገባ የማይቀር ክስተት /reality/ ነው ብለዋል፡፡ የግብፅ የድርድር ግብ መሆን ያለበትም ግድቡን ማስቆም ሳይሆን ሁለቱም ወገኖች ተጠቃሚ በሚሆኑበት መንገድ ላይ ሊሆን እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ “የአስዋን ግድብ ለኛ አንደሚያስፈልገን ሁሉ የህዳሴዉ ግድብም ለኢትዮጵያውያን ብሄራዊ ሃብታቸው ነዉ” ሲሉ ነው እዉነታውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ የቆረጡት፡፡ አምባሳደሩ አሁን ኢትዮጵያ ያደረገችው ነገር ዱብ እዳ ሳይሆን ካለፈው ህዳር ጀምሮ የምናውቀው ነው ብለዋል፡፡
በሁሉም መድረኮቻችን ኢትዮጵያ በኛ ላይ ጉዳት እንደማታስከትል ደጋግማ አረጋግጣልናለች፤ እኛም ይህንኑ አምነን ተቀብለናል ያሉት አምባሳደሩ ግብፅ ሶስቱም ወገኖች ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አሰራር እየፈለገች መሆኗን ተናግረዋል፡፡

እኔ የነዚህን ባለስልጣናት ንግግር በአወንታዊ መልኩ ነው ያየሁት፡፡ ምክንያቱም ቢያንስ ኢትዮጵያ እነሱን የመጉዳት ሃሳብ እንደሌላት መረዳታቸዉን ገልፀውልናል፡፡ የጋራ ተጠቃሚነት መርህ ቀስ በቀስ ቅቡል እየሆነ መምጣቱን አመላካች አስተያየት ነው፡፡
ሆኖም የሀገሪቱና የአለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘገባ አሉታዊ ነው፡፡ መገናኛ ብዙሃኑ ከግድቡ ጋር ያሉ አወንታዊ ጎኖችን ዘወር ብለዉ እንኳን ሳያዩ ሊያስከትል ይችላል ብለዉ ባሰቡት ተፅዕኖ ላይ ብቻ ነዉ ያተኮሩት፡፡
ባለስልጣኖቹ ከተናገሩት ውስጥ ሲመርጡ እንኳን ይህንኑ ፍላጎታቸውን የሚያሟላላቸዉን ንግግር ብቻ እንጅ በመቻቻልና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ያተኮሩትን አገላለፆች በተደጋጋሚ ዘለዋቸዋል፡፡ ለምሳሌ ያክል ሞሃመድ ባሃ ኢልዲን ግብፅ በጥቅሟ ላይ የሚመጣን ማንኛውንም አይነት ፕሮጀክት እንደማትደግፍ መግለፃቸውን ሲያራግቡ በግብፅ ላይ የተደቀነ አደጋ የለም ማለታቸውን ግን ብዙዎቹ አድበስብሰውት አልፈዋል፡፡
ሌላው የሚጠበቅ ግን ቢሆንም መታወቅ ያለበት የግብፅ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቋም ነዉ፡፡ ፓርቲዎቹ ይህንን ጉዳይ ለፖለቲካ ጥቅም ማግኛ ሲጠቀሙበት ተስተውለዋል፡፡ እነሱ እንደ ጠንካራና ለግብፅ ህዝብ የቆሙ፤ ሙስሊም ብራዘርሁድ የሚመራው መንግስት ደግሞ እንደ ልፍስፍስና የህዝቡን ጥቅም አሳልፎ የሰጠ አድርገው አሳይተዋል፡፡ የናሽናል ሳልቬሽን ፍሮንቱ ኤል ባራዲ በቅርብ ሰዓት በግል ቲዊቱ የሲና በረሃና ኢትዮጵያ መተላለቅን የሚያስከትሉ አደገኛ የቀውስ ምንጭ እንደሆኑ ተንብየዋል፡፡ ይችን ነገር ከኛ ሃገር ተቃዋሚዎች የኮረጇት ሳትሆን አትቀርም፡፡ በነገራችን ላይ የኛዎቹ እስካሁን ድምፃቸዉ አልተሰማም፡፡ የአባይ መንገዱን መቀየር አልሞቃቸውም፤ አልበረዳቸውም፡፡
ይህ በንዲህ እንዳለ የሱዳኑ የውሃ ሃብትና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር ሞሃመድ ሃሰን በጉዳይ ላይ ለመምከር ወደ ካይሮ ሄደዋል፡፡ እዛ እንደደረሱም ከግብፁ አቻቸው ጋር ተመካክረዋል፡፡ ምን እንደዶለቱ ግን እስካሁን ወሬ አላገኘሁም፡፡ ወደ ሱዳን ከገባሁ አይቀር በዚሁ የሱዳን ሁኔታ እንመልከት፡፡
በግብፅ የሱዳኑ አምባሳደር ከማል ሃሰን የአባይ ወንዝ አቅጣጫ የመቀየር ዜና አስደንጋጭ እንደሆነና ሱዳንና ግብፅ የአረብ ሊግን ጣልቃ ገብነት ሊጠይቁ እንደሚችሉ ተናግረዋል በሚል ትናንት በርካታ መገናኛ ብዙሃን ተቀባብለውት ነበር፡፡ ሆኖም ከምሽት ጀምሮ በአንዳንድ የግብፅ ጋዜጦችና በሱዳኑ ሱዳን ትሪቡን ድረ ገፅ የወጣ ዘገባ አምባሳደሩ ይህንን ማለታቸውን የሚያስተባብል ነው፡፡

የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እኛ እንዲህ አይነት ንግግር ካፋችን አልወጣም ብሏል፡፡ ኢትዮጵያ እያደረገች ያለችው ነገር በሱዳን ላይ ምንም ጉዳት እንደሌለው አረጋግጠናል፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ሁላችንም ተጠቃሚ በምንሆንበት ነገር ላይ ከኢትዮጵያም ሆነ ግብፅ ጋር ለመተባበር ዝግጁ ነን ሲል አቋሙን አሳውቋል፡፡
እስኪ አሁን ደግሞ ትናንት ምሽት በአልጀዚራ ስለተላለፈዉ ፕሮግራም ላንሳ፡፡ በኢንሳይድ ስቶሪ ፕሮግራም ላይ ከአዲስ አበባ የመንግስት ኮሚዪንኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምዖን፤ ከካይሮ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዋ ላማ ኤል ሃሎና ከለንደን ደግሞ ደራሲዋ ሊዮ ፓስካል ቀርበዋል፡፡
የፕሮግራሙ አዘጋጅ ገና ሲጀምር የህዳሴውን ግድብ በግብፅ ህልውና ላይ የተደቀነ አደጋ አድርጎ ነው ያቀረበው፡፡ የግብፅ ህዝብ በ2050 /በነሱ አቆጣጠር/ 150 ሚሊዮን ስለሚደርስ ግብፅ ተጨማሪ 21 ቢሊዮን ኪዉቢክ ሜትር ውሃ ያስፈልጋታል፤ ግድቡ ግን እንኳን ይህን እድል ሊሰጣት 18 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ያሳጣታል ሲል በመደምደም ይነሳል፡፡ የሃይል ማመንጨት አቅሟንና የግብርና ምርት መጠኗንም ይቀንሰዋል፤ በዚህም ሚሊዮኖች ለረሃብ ይጋለጣሉ ይላል ጋዜጠኛዉ፡፡

አቶ በረከት በሰጡት ምላሽ ታዲያ እንደማስበው የኢትዮጵያ ፍላጎት በግብፅም ሆነ ሱዳን ላይ ይህን ያህል ጭንቅ መፍጠር ሳይሆን የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት ነው አሉ፡፡
ጋዜጠኛዉ “ፍላጎታችሁ ጉዳት ማድረስ ላይሆን ይችላል ግን ሂደቱ ይህን ጣጣ ሊያመጣ ይችላል” ሲል አቋረጣቸው፡፡ በረከትም ሂደቱ የሚያስከትለዉ እንደውም የተሻለ የዉሃ መጠን ነዉ፡፡ ምክንያቱም እኛ በአካባቢያችን የምናከናውነው የተፈጥሮ ሃብት እንክብካቤ ስራ የከርሰ ምድር ዉሃ መጠንን የሚያሳድግ ነው ሲሉ ተከራክረዋል፡፡
በዚህ ግዜ ጋዜጠኛው ሊዎ ፓስካልን ግብፅ የሱዳንን መሬት ተጠቅማ በኢትዮጵያ ላይ የሃይል እርምጃ ልትወስድ የምትችልበት እድል እንዳለ ጠየቃት፡፡ እርሷም ስትመልስ ግብፅ ይህን ስልት ቀድማም ትጠቀምበት እንደነበር አስታውሳለች፡፡ በተለይም ሶማሊያንና ኤርትራን በመጠቀም ኢትዮጵያን የማዳከም ስልት ትከትል እንደነበር አውስታለች፡፡ አሁን ግን የኢትዮጵያ ጡንቻ በአካባቢው እየፈረጠመ መሆኑን ታነሳና የጦርነት አማራጭ ለግብፅ አዋጭ እንዳልሆነ በተዘዋዋሪ አስረድታለች፡፡
ጋዜጠኛው ውሃን እንደጦር መሳሪያ አድርጎ ማየቱ ያላስደሰታቸዉ አቶ በረከት “እኛ ዉሃ ያጣላናል ብለን አናስብም፡፡ ይህ አንተ የምትለዉም ግዜ ያለፈበት ተረት ነዉ” ብለውታል፡፡ እንደ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ወጭውን ብቻዋን ትሸፍነው እንጅ ጥቅሙ የሁሉም ሀገሮች ነው፡፡ ግብፅም ሆነች ሱዳን በበጋ ወራት ሳይቀር ወጥነትና ብዛት ያለው ዉሃ ሊያገኙ እንደሚችሉ የተከዜው ግድብ ለሰሜን ምስራቅ የሱዳን አካባቢዎች ያስገኘዉን ጥቅም በአብነት በማንሳት አብራርተዋል፡፡
በቅኝ ግዛት ወቅት የተፈረሙ ስምምነቶች ኢትዮጵያን ያገለሉ እንደሆኑና ይህንን በመቀየር ኢትዮጵያም ሆነች ሌሎቹ ሃገራት በጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አሰራር መዘርጋት እንደሚገባ ተከራካሪዎቹ አንስተዋል፡፡ ፓስካ “ኢትዮጵያ የድርሻዋን ካልተጠቀመችማ ለውሃው /ለወንዙ/ ደህንነት ለምን ትጨነቃለች?” ስትል መልሳ ጠይቃለች፡፡ ኤል ሃሎ በበኩሏ የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ንግግርን በማስታወስ ግድቡ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይሆን የአካባቢው ሃብት እንደሆነ አሳይታለች፡፡
በአጠቃላይ ሲታይ ውይይቱ መግባባት የሰፈነበት ነበር፡፡ ሆኖም ከኢትዮጵያው ሚኒስትር በስተቀር ሌሎቹ ጉዳዩ በቀጥታ የማይመለከታቸውና የመወሰን ስልጣን የሌላቸዉ መሆኑ የውይይቱን ፋይዳ ያሳንሰዋል፡፡ ውይይቱ በሶስቱ ሃገራት ከፍተኛ ባለስልጣኖች መካከል ቢሆን ይሻል ነበር፡፡ ነገር ግን ሱዳንና ግብፅ በአሁኑ ሰዓት /ቢያንስ የገምጋሚው ቡድን ሪፖርት ይፋ እስኪሆን/ ለመነጋገር ዝግጁ የሆኑ አይመስልም፡፡