Wednesday, December 4, 2013

ሰንደቅ ዓላማ

ከከበደ ሚካኤል (ታሪክና ምሳሌ ፩ኛ መጽሐፍ የተወሰደ)
ሰንደቅ ዓላማ የነጻነት ምልክት፣ የአንድ ህዝብ ማተብ፣ የኅብረት ማሰርያ ጥብቅ ሐረግ ነው።
              "ተመልከት ዓላማህን፤ ተከተል አለቃህን"
ነጋሪቱ እየተጎሰመ፣ ሠራዊቱ እየተመመ ሲሄድ ሰንደቅ ዓለማ ትምህርተ ኃይል፣ ትምህርተ መዊዕ ነው።
ሰንደቅ ዓላማችን አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ሦስት ቀለማትን ይዟል። ምሳሌአቸውም አረንጓዴው ተስፋ፣ ልምላሜ ሃብት፤ ቢጫው ሀይማኖት፣ አበባና ፍሬ፤ ቀዩ ፍቅር፣ መሥዋዕትነትና ጀግንነት ነው።

No comments:

Post a Comment