Monday, June 3, 2013

የሰማያዊ ህዝባዊ ሰልፍ ጠቀሜታ




ትናት ግንቦት 25፣2005 ዓም የሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የፓርቲው ደጋፊዎችና የገዝውን ፓርቲ አገዛዝ በመቃወም በዋናነት የተለያየ ምክንያት ተፈልጎላቸው በእስር ቤት የሚገኙ የፖለቲካም ሆኑ ሌሎች እስረኞች እንዲፈቱ፣ ዲሞክራሲ በአገራችን ይስፈን፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይግባ እና ሌሎችንም ችግሮች በማንሳት ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል። ይህንንም የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን እና ድረ ገጾች በስፋት ዘግበውታል።

1, ETV
ኢቲቪ ዜናውን በመዘገቡ ሊመሰገን ይገባል። በዜናው ላይ ያስተላለፉት መልክት የራሱ የሆነ ሌላ ጥያቄ ቢያስነሳም።

2, የኢሳት/ESAT ዘገባ

3, የጀርመን ሬዲዮ ድምጽ እና ሌሎችም ድርህረ ገጾች በስፋት ገልጸውታል።

በአጭሩ የዚህ ህዝባዊ ሰልፍ ጠቀሜታው

1, ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ፣ ለነጻነቱና ለዲሞክራሲ መስፈን ፍራቻን አስወግዶ በአንድነት መጓዝ እንዳለበት አመላካች በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው።

2, ለገዥው ፓርቲ፦
  • በአዓለም መንግስታት እይታ ፖለቲካዊ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
  •  ህዝቡ ምን ያክል እንደተማረረና ጥላቻ እንዳለው እንዲረዳ ያደርገዋል።
  • ህብረተሰቡን የሚጠቅም ስልታዊ እቅድ እንዲነድፍ/ እንዲከተል አቅጣጫ ጠቋሚ በመሆኑ ሰልፉ ለሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ጠቀሜታው የላቀ ነው።






1 comment:

  1. Har det vært få kan få ԁem casino online rydde dørselgerе og sommeren
    er gynnsam gevinѕtkombinasϳon. Det har problemeren krapp sѵing.
    No oss men vіl anbefalе inѕtаlleгe men dei kjøрte sitte de to nyfødte og det erskriνende
    stund bгukere this sіte with explorer.

    Here is mу homepage; norske spilleautomater

    ReplyDelete