Wednesday, May 22, 2013

የባህርዳር ሀዘን

ሰሞኑን ባህር ዳር ሀዘን በሀዘን ተደራርቦባታል። ምንም እንኳ ሀዘኑ በተለያየ መልኩ ቢከሰትም አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ተደጋጋሚ አደጋ በመከሰቱ ሀዘኗን እጥፍ ድርብ አድርጎባታል።
 1, ግንቦት 4 /2005 ዓም  በአንድ  ፌደራል  ፖሊስ   በመንግሥት  መገናኛ 12  ሰዎችን፤  በኢሳትና  በተለያዩ ድህረ ገጾች ደግሞ ከ 16 እስከ 18 ሰወችን መግደሉ ባህርዳርን በሀዘን  ትገኛለች።

 የኢሳት ምንጭ/ESAT

2, ግንቦት 12/2005 ዓም ደግሞ በልጆቿ መሞት እንበዋን ሳታብስ ሌላ ተጨማሪ ልብ የሚሰብር ሀዘን፤
ከምእራብ ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ ልዩ ስሙ ቁንዝላ ተነስቶ ወደ ሰሜን ጎንደር ጣቁሳ ወረዳ ደልጊ ከተማ 101 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው ጀልባ ግንቦት 12/2005 ከቀኑ 10:30 በጋጠመው ድንገተኛ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
ከአደጋው ከ90 በላይ ሰዎች ህይወት ሊተርፍ መቻሉንና እስከ አሁን የጠፉ ሰዎችን የማፈላለግ ስራም እየቀጠለ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡/ምንጭ፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን/
3, ትናንት ምሽት ማለትም በ13/2005 ዓም በባህርዳር ከተማ ውስጥ የሚገኝ የጅምላ ንግድ አካፋፋይ ድርጅት/ጅንአድ መቃጠሉን የተለያዩ  መገናኛ ብዙሀንና ድህረ ገጾች e እየገለጹ ይገኛሉ።
የኢሳት ምንጭ/ESAT 

እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን፤ለአዘኑት መጽናናትንና መረጋጋትን ይስጥልን፡ አሜን!

1 comment: